1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስጋት

ዓርብ፣ ጥቅምት 19 2014

ከሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች ለትምህርት ወደ ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የሄዱት አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬሌ የሰጡት ተመራቂዎች «ለምረቃ መብቃታችን ትልቅ ደስታ ነው ፤ ነገር ግን ከምረቃ በኋላ የት ነው የምንሄደው?» የሚለው ትልቅ ስጋት እንደሆነባቸው ተናግረዋል።

Äthiopien Haramaya Universität
ምስል፦ DW/Mesaye Tekelu

«ከሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች የመጡ ተማሪዎች»

This browser does not support the audio element.

ከሰሜን የሀገሪቱ አካባቢዎች በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ከምረቃ በኋላ ወደ አካባቢያቸው ለመሄድ ያለው የሰላም ሁኔታ እንዳሳሰባቸው ገለፁ። ከቤተሰብ ጋር ከተገናኙ መቆየታቸውን እና አሁንም የደስታቸውን ጊዜ ከቤተሰብ ጋር ማሳለፍ ባለመቻላቸው ማዘናቸውን የጠቆሙት ተማሪዎች መንግሥት ለተጋረጠባቸው ስጋት መፍትሄ እንዲያፈልግ ጠይቀዋል። ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎቹ ችግር በሚፈታበት ሁኔታ ላይ ከትምህርት ሚንስቴር ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ተናግሯል።

መሳይ ተክሉ 

ሸዋዬ ለገሠ

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW