1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ትኩረት በአፍሪቃ 12.08.2023

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 6 2015

ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ በቅርቡ ሕገ መንግሥታዊ ለውጥ እንዲመጣ ዜጎቿ ድምፅ ሰጥተዋል።95% መራጮች ደግፈውታል የተባለው ይህ ህዝበ ውሳኔ ፤ተቺዎች እንደሚሉት ፕሬዚዳንቱን ለዕድሜልክ ስልጣን ላይ የሚያቆይ ነው።

Zentralafrikanische Republik | Abstimmung über neue Verfassung
ህዝበ ውሳኔ በህገመንግስት ለውጥ ላይ በመካከለኛው አፍሪቃ ሪፐብሊክምስል፦ Barbara Debout/AFP

የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ህገመንግስታዊ ለውጥ

This browser does not support the audio element.


በወርቅ እና በአልማዝ  በበለፀገችው አፍሪቃዊት ሀገር ፤ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ በቅርቡ ሁከትና ብጥብጥን የሚያነግስ  ሕገ መንግሥታዊ ለውጥ እንዲመጣ ዜጎቿ ድምፅ ሰጥተዋል። ይህ አዲስ ህዝበ ውሳኔ እና ለህገ-መንግስታዊ ለውጥ ፕሬዝዳንት ፋውስቲን-አርቼንጅ ቱአዴራ ለሶስተኛ ጊዜ የስልጣን ዘመናቸውን እንዲያራዝሙ የሚያደርግ በመሆኑ በሀገሪቱ ውዝግብ አስከትሏል።ፕሬዚዳንቱ ግን ደስተኛ ናቸው።
«የዜግነት ግዴታን የመወጣት ስሜት ነው። የተሳካልኝ ሆኖ ይሰማኛል። ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የመጡ ወገኖቼ ድምጽ ለመስጠት እንደመጡ ሁሉ የዜግነት ግዴታዬን ተወጥቻለሁ። ኩራት ይሰማኛል. ምክንያቱም የማዕከላዊ አፍሪካ ሕዝብ ጥያቄ ነበር።»
 አዲሱ ህግ አሁን ያለውን የሁለት ጊዜ ገደብ በመሻር የፕሬዚዳንቱን ስልጣን ከአምስት ወደ ሰባት አመታት ያራዝመዋል።ባለሁለት ዜግነት ያላቸው ፖለቲከኞች ሌላውን ካልተው በስተቀር ለፕሬዚዳንትነት እንዳይወዳደሩም ይከለክላል።
95% መራጮች ደግፈውታል የተባለው ይህ ህዝበ ውሳኔ ፤ተቺዎች እንደሚሉት የምርጫው ሂደት ግልፅነት የጎደለው እና በቂ ምክክር ያልተደረገበት ነው።በምርጫው የተገኘው ውጤትም 10 በመቶ ዝቅተኛ ነበር።የመአከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ምርጫ
በጎርጎሪያኑ ሀምሌ 30 ቀን 2023  የተካሄደውን ይህ ህዝበ ውሳኔ፤ ፕሬዝዳንቱ የፈለጉትን ያህል ጊዜ እንዲወዳደሩ የሚፈቅድ ሲሆን፤ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና አንዳንድ የሲቪል ማህበረሰብ ቡድኖች  ፕሬዝደንት ቱዋዴራን እድሜልካቸውን በስልጣን ላይ እንዲቆዩ ለማድረግ የተነደፈ "ህገ መንግስታዊ መፈንቅለ መንግስት" ሲሉ  ይተቹታል። የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ክሬፒን ምቦሊ ንጎምባ፣ ዜጎች በምርጫው እንዳይሳተፉም አስቀድመው ጠይቀው ነበር።
«ህገ ወጥ የሆነውን ሂደት መቀላቀል ለህገ-ወጥ ሂደት ህጋዊነት መስጠት ነው።  ያንን ማድረግ የምንችልበት ምንም መንገድ የለም። ሂደቱ በሙሉ ህገወጥ መሆኑን ሰዎች ማስታወስ አለባቸው። በእርግጥ የዚህ ተቋም ፕሬዚዳንት መመሪያዎችን ለማግኘት ወደ ሩሲያ ሄዷል።.የአሁኑ የሕገ መንግሥት ፍርድ ቤት ህጋዊ ፕሬዚዳንትም መመሪያ ለመውሰድ ወደ ሩሲያ ሄዷል። እኛ ግልፅ የምናደርግበት ምንም መንገድ የሌለው የተበላሸ ሂደት ነው። ቱአዲር  ለማሳካት እየሞከሩ ያለት አምባገነን ስርዓት ለመመስረት ነው።»
ፕረዚደንት ፋውስቲን-አርሴንጅ ቱዋዴራ በሩሲያ የዋግነር ቅጥረኞች ይደገፋሉ ከህዝበ ውሳኔው በፊት ተጨማሪ ተዋጊዎች ደርሰዋል ሲሉም ይከሷቸዋል።
ኢቫሪስቴ ንጋማና-የህዝበ ውሳኔው ብሔራዊ ዘመቻ ዳይሬክተር ግን ክሱን አይቀበሉትም።እንዲያውም ትችቱ ህዝብን መናቅ ነው ይላሉ።
« የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ህዝቦች በሙሉ በሩሲያውያን ተታለዋል ትላለህ... አይሆንም! ለመካከለኛው አፍሪካ ህዝብ ትንሽ ክብር እንዲኖራችሁ በትህትና እጠይቃችኋለሁ። ከህዝብ በላይ የሆነ ተቋም የለም። በሕዝብ የተጠየቀውን በጽሑፍ መደበኛ  ከማድረግ ውጪ ሌላ ዓላማ የለንም።»
የዋግነር ሃይሎች አሁንም ሰፊ የሀገሪቱን አካባቢዎች የሚቆጣጠሩትን አማፂ ቡድኖችን ለመዋጋት ፕሬዝዳንት ቱዋዴራን ሲደግፉ የጦር ወንጀል ፈጽመዋል ተብለውም ይከሰሳሉ።በማዕድን እና በእንጨት ኢንዱስትሪዎች ላይም ድርሻቸው ከፍተኛ ነው ይባላል። 
ወደብ አልባዋ ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ከጠቅላላው ህዝብ ሲሶውን ከመኖሪያ ቤቱ ባፈናቀለ የዕርስ በዕርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኝ እና 60 በመቶ ህዝቧ በድህነት የሚኖርባት ሀገር ነች።

አንድ ወጣት በማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ምስል፦ Alexis Huguet/AFP/Getty Images
የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ፕሪዚደንት ፋውስቲን አርቼጌ ቱዶራ እና የሩሲያው ፕሬዚደንት ብላድሚር ፑቲንምስል፦ Sergei Chirikov/AP Photo/picture alliance
ክሪፔን ምብሊ ጎምባ የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ የተቃዋሚ ፓርቲዎች አስተባባሪ ምስል፦ DW
የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ፕሬዚደንት ፋውስቲን አርቻንጌ ቱዴራ ምስል፦ Barbara Debout/AFP/Getty Images

ሀገሪቱ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ሕገ መንግስታቸውን ከለወጡት ቡሩንዲ፣ኡጋንዳ እና ሩዋንዳ ከመሳሰሉ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ተቀላቅላለች።የብሩንዲ የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክና የማሊ ቀውስ
ፕሬዝዳንቱ "የህዝቡን ፍላጎት" እየተከተልኩ ነው ይላሉ።ነገር ግን ጉዳዩ በሀገሪቱ ዲሞክራሲ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች  ፣እንዲሁም ሩሲያ  በሌላ የአፍሪቃ ሀገር ጉዳይ የተጫወተችው ሚና መልስ አላገኘም።

 


ፀሀይ ጫኔ
እሸቴ በቀለ 

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW