1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የለጋሽ ድርጅቶች ዕርዳታ መቀነስ በጋምቤላ በሚገኙ ስደተኞች ላይ ያደረሰው ተጽዕኖ

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 3 2017

ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ ርዳታ መቋረጥ በኢትዮጵያ ጋምቤላ ክልል የሚገኙ ስደተኞችን ኑሮ እንዲያሽቆለቁል ማድረጉን ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን አስታውቋል። በክልሉ ከሚገኙ ሰባት የስደተኞች መጠለያዎች በአራቱ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት በመቋረጡ የ80,000 ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆነ ሕጻናት ሕይወት የሚያሰጋ ችግር ተጋልጠዋል።

የድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን መለያ
በጋምቤላ አራት የስደተኞች መጠለያዎች የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት በመቋረጡ 80,000 ሕጻናት ለችግር ተጋልጠዋል ምስል፦ Martial Trezzini/KEYSTONE/picture alliance

በጋምቤላ አራት የስደተኞች መጠለያዎች የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት በመቋረጡ 80,000 ሕጻናት ለችግር ተጋልጠዋል

This browser does not support the audio element.

ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን የተባለው የግብረ ሰናይ ድርጅት የእርዳ መቋረጥ በጋምቤላ ክልል በሚገኙ የስደተኞችን አኗኗር ፈጣኝ እያደረገ ነው ሲል አመልክተዋል፡፡ ቁልፍ የተባሉ እንደ ዩኤስ፣አይ.ድ ያሉ ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታ መቋረጥ በጤና፣ትምህርት እና በሽታ መከላከል እያዳከመ መሆኑን ጠቅሶ በዚህም 80ሺየሚደርሱ ህጻናት ለተመጣጠነ የምግብ እጥረት መጋለጣቸውን አመልክተዋል፡፡የስዴተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት በበኩሉ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመቅረፍ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡

በ4 ካምፕች 80ሺ የሚደርሱ ከ5 ዓመት በታች ህጻናት ለምግብ እጥረት ተጋልጠዋል

በጋምቤላ ክልል ከ395ሺ በላይ ስደተኞች በ7 የተለያዩ ጣቢዎች እንደሚገኙ የገለጸው የድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን ኩሌ በተባለው አንዱ ስደተኞች ጣቢያ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡ ድርጅቱ ከሁለት ቀን በፊት ባወጣው ዘገባም የዓለማ አቀፍ ድርጅቶች እርዳታ መቋረጥና እና መቀነስ በስደተኞች ላይ በተለያዩ ዘርፍ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡

መጠኑ የቀነሰው ሰብአዊ እርዳታ በትግራይ ክልል

ሶስት ስደተኞችን ምስክረነትን ጠቅሶ ደርጅቱ እንዳመለከተው ሰብአዊ ድጋፍ መቀነሱ ስደተኞችን ኑሮ ፈታኝ ማድረጉ እና ለህክምና እርዳታ ከአንዱ ጣቢያ ረጅም ርቀት በመጓዝ ኩሌ በተባለው ጣቢያ እርዳታ እያገኙ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡ ከዚህ ቀደም አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ስፍራውን መልቀቃቸውን ተከትሎ በጤናው ዘርፍ የሚስተዋለውን ክፈተት ከፍተኛ መሆኑን ዘገባው አመልክተዋል፡፡

በጋምቤላ ክልል ከሚገኙ መጠለያዎች መካከል በ4 ካምፕች 80ሺ የሚደርሱ ከ5 ዓመት በታች ህጻናት ለምግብ እጥረት ተጋልጠዋልምስል፦ Negassa Dessalegn/DW

በኢትየጵያ ከ1.1 ሚሊዩን በላይ ስደተኞችን ተመዝግቦ እንደሚገኙ ያስታወቀው የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎትም የተስተዋሉ ከፍተቶችን ለመቅረፍ ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ተገቢውን ድጋፍ መስጠት እንዳለበት አመልክተዋል፡፡ የስደተኞችና ተመላሾች ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሙሉዓለም ደስታ ለጋሽ ድርጅቶች በተለይም አብዛኛውን ሰብአዊ ድጋፍ የሚሰጡ እንደ ዩኤስ. ኤድ ያሉ ድርጅቶች እርዳታ መቀነስ በጤና እና ትምህርት ላይ ተጽህኖ ማሳደሩን አቶ ሙሉዓለም ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም በጤና እና ትምህርት ላይ እያደረሰ ያለውን ተጽህኖ አብራርተዋል፡፡

በጋምቤላ አዲስ የስደተኞች ጣቢያ እየተቋቋመ ነው

ሀገርቷ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኞችን እያስተናገደች እንደሚትገኝ በመግለጽ ዓለም አቀፍ ማህሰረብ እና ተቋማት ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ አለባቸው ብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም ድጋፍ ለማድረግ ቃል ከገቡት መካከልም ሁለት ሀገሮች ኔዘርላንድ እና ጀርመን ድጋፍ ማድረጋቸውንም ጠቁመዋል፡፡

በደቡብ ጎንደር ዞን በድርቅ ምክንያት ከ175ሺህ በላይ ሠዎች እርዳታ ይፈልጋሉ

በጋምቤላ ክልል ከሚገኙት 7 የስደተኞች ጣቢዎች በተጨማርም በቅርቡ ከደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚሻገሩ ስደተኞች ቁጥር መጨመርን ተከትሎ አዲስ የስደተኞች ጣቢያ እየተቋቋመ እንደሚገኝ አቶ ሙላለም ደስታ አመልክተዋል፡፡

የድንበር የለሽ ሀኪሞች ቡድን በስደተኞች ካምፕ አስፈላጊ የሆኑ የጤና አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ የገለጸ ሲሆን ከሌሎች ተዋናዮች አስቸኳይ ድጋፍና ጣልቃ ገብነት ካልተገኘ ቀውሱ ተባብሶ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት የበለጠ

አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል ሲል ስጋቱን ገልጸዋል፡፡ የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ችግሮችን ለመቅረፍ ከተቀባይ ማህበረሰብ በተጨማረ ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት ሊያደርግ እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡

ነጋሳ ደሳለኝ

እሸቴ በቀለ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW