1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የላይቤሪያ ፕሬዚደንት የኢትዮጵያ ጉብኝት

ማክሰኞ፣ የካቲት 21 2009

የላይቤሪያ ፕሬዚደንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ዛሬ በኢትዮጵያ የአራት ቀን ይፋ ጉብኝት ጀመሩ። ፕሬዚደንት ሰርሊፍ በብሔራዊ ቤተመንግሥት ከፕሬዚደንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ እና ከጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በሀገሮቻቸው መካከል ስላለው ግንኙነት እና ስለአህጉራዊ ጉዳዮች ተወያይተዋል።

Äthiopien Besuch Präsidentin Liberia Ellen Johnson Sirleaf
ምስል picture-alliance/abaca/M. W. Hailu

Ber. AA(Pr. Sirleaf Äthiopien Besuch) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

ከውይይቱ በኋላ ፕሬዚደንት ሰርሊፍ  ከጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በሰጡት በአፍሪቃው ያለውን የንግድ ልውውጥ ማሻሻል እንደሚያስፈልግ  ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያምም በተመድ የፀጥታው  ምክር ቤት ተለዋጭ አባልነ የሆነችው ኢትዮጵያ አፍሪቃን በሚመለከቱ፣ የአየር ንብረት ለውጥን በመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ የአህጉሩን የጋራ ድምጽ እንደምታሰማ እና ከላይቤሪያም ጋር በቅርብ እንደምትሰራ አስታውቀዋል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

አርያም ተክሌ

አዜብ ታደሰ 


 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW