1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ውዝግቦችአውሮጳ

የሐንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር የሩሲያ ጉብኝትና የዩክሬን ጦርነትን ለማቆም የሚደረገው ጥረት

ዓርብ፣ ኅዳር 19 2018

በዩክሬን በመካሔድ ላይ የሚገኘውን ጦርነት ለማቆም የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በተጧጧፈበት በዚህ ወቅት የሐንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን የሩሲያ እና የአሜሪካ መሪዎች የሚገናኙበት ስብሰባ በቡዳፔስት እንዲካሔድ ጋብዘዋል። ትራምፕ ያቀረቡት ምክረ ሐሳብ በአሜሪካ፣ ሩሲያ፣ ዩክሬን እና የአውሮፓ ዲፕሎማቶች ንግግር እየተደረገበት ይገኛል።

 የሐንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን እና የሩሲያ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በሞስኮ በተገናኙበት ወቅት እጅ ለእጅ ተጨባብጠው ይታያሉ።
በዩክሬን በመካሔድ ላይ የሚገኘውን ጦርነት ለማቆም የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በተጧጧፈበት በዚህ ወቅት የሐንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን የሩሲያ እና የአሜሪካ መሪዎች የሚገናኙበት ስብሰባ በቡዳፔስት እንዲካሔድ ጋብዘዋል። ምስል፦ Alexander Nemenov/Pool/AFP

የሐንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን የሩሲያ ጉብኝትና የዩክሬን ጦርነትን ለማቆም የሚደረገው ጥረት

This browser does not support the audio element.

የሐንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን የሩሲያ እና የዩናይትድ ስቴትስ ስብሰባ በቡዳፔስት እንዲካሔድ በድጋሚ ጥሪ አቀረቡ። ፕሬዝደንቱ ጥሪውን ያቀረቡት ዛሬ ከሩሲያ ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሞስኮ በተወያዩበት ወቅት ነው። 

ለግብዣው ምሥጋናቸውን ያቀረቡት ቭላድሚር ፑቲን የአሜሪካው አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ የመገናኘት ሐሳብ እንዳቀረቡ ገልጸዋል። ፑቲን በዩክሬን የሚካሔደውን ጦርነትለማቆም እየተደረጉ የሚገኙ ድርድሮች ተገቢውን ውጤቶች ካስገኙ ከዶናልድ ትራምፕ ለመገናኘት እንደሚዘጋጁ ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያ አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን የሚገናኙበትን ስብሰባ ሐንጋሪ ታዘጋጃለች ተብሎ ነበር። ይሁንና በቡዳፔስት ይካሔዳል ተብሎ የነበረው የሁለቱ መሪዎች ስብሰባ ጊዜ ማባከን እንዲሆን አልፈልግም ያሉት ትራምፕ እንደማይሳተፉ አስታውቀው ተሰርዟል። 

የሐንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን ወደ ሩሲያ ከማቅናታቸው በፊት ኦርባን በዩክሬንየሚካሔደውን ጦርነት ለማቆም የቀረቡት“የሰላም ምክረ-ሐሳቦች ወደ ተኩስ አቁም እና ሰላም ይመራሉ ብለን እጅግ ተስፋ እናደርጋለን” ብለው ነበር። ቀኝ ዘመም የፖለቲካ ርዕዮት የሚከተሉት ኦርባን ወደ ሞስኮ ካቀኑባቸው ጉዳዮች አንዱ ሩሲያ ለሐንጋሪ በምታቀርበው ድፍድፍ ነዳጅ እና ጋዝ ላይ ለመነጋገር ነበር።

ሐንጋሪ የአውሮፓ ኅብረት እና የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) አባል ሀገራት አንዷ ብትሆንም ቪክቶር ኦርባን ለፑቲን የጠበቀ ግንኙነት አላቸው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ሩሲያ ያቀኑት የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ልዑክ ስቲቭ ዊትኮፍ በሚቀጥለው ሣምንት በሞስኮ የዩክሬን ጦርነትን ለማቆም በተጀመረው አዲስ ጥረት ላይ ከፑቲን ለመነጋገር ወደ ሞስኮ ያቀናሉ ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። 

የሐንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን የሩሲያ ጉብኝት እና የዩክሬን ጦርነትን ለማቆም የሚደረገውን ጥረት በተመለከተ ወደ ገበያው ንጉሤን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ገበያው ንጉሤ
እሸቴ በቀለ
ነጋሽ መሐመድ 
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW