1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሐገር ሽማግሌዎችና የትግራይ ክልል ፖለቲከኞች ዉይይት

ሚሊዮን ኃይለ-ሥላሴ
ማክሰኞ፣ ሐምሌ 22 2017

ከኢትዮጵያ 12 ክልሎች እና 2 የከተማዋ አስተዳደሮች የተወከሉ 50 የሃገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ትላንትና ዛሬ ከክልሉ የአስዳደር አካላት፣ የተለያዩ ፓርቲ ፖለቲከኞች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና ሌሎች የተወያዩ ሲሆን ዋና አጀንዳቸውም ሰላም ማፅናት ላይ ማድረጋቸው ተገልጿል።

የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጄነራል ታደሰ ወረደ በትግራይ በኩል የሚጀመር ጦርነት በፍፁም አይኖርም ሲሉ ለሽማግሌዎቹ ተናግረዋል።
ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የተዉጣጡ የሐገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት አባቶች ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ባለሥልጣናት ጋር መቀሌ ዉስጥ ተወያይተዋል።ምስል፦ Million Haileselassie/DW

የሐገር ሽማግሌዎችና የትግራይ ክልል ፖለቲከኞች ዉይይት

This browser does not support the audio element.

በህወሓት እና የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት መካከል የተፈጠረው መካረር ለመሸምገል ያለሙ የተባሉ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ትላንት ወደ በመቐለ በመጓዝ ከክልሉ ፖለቲከኞች ጋር ተወያዩ። የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ በትግራይ በኩል የሚጀመር ጦርነት በፍፁም አይኖርም ሲሉ ለሽማግሌዎቹ ተናግረዋል።

ትላንት መቐለ የመጡት ከኢትዮጵያ 12 ክልሎች እና 2 የከተማዋ አስተዳደሮች የተወከሉ 50 የሃገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ትላንትና ዛሬ ከክልሉ የአስዳደር አካላት፣ የተለያዩ ፓርቲ ፖለቲከኞች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና ሌሎች የተወያዩ ሲሆን ዋና አጀንዳቸውም ሰላም ማፅናት ላይ ማድረጋቸው ተገልጿል። በትላንትናው ዕለት ከትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ባለስልጣናት የተወያዩት እነዚህ ልኡካን ግጭት መልሶ እንዳይቀሰቀስ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል። ከእነዚህ ልኡካን መካከል አንዱ፥ ያለፈው ጦርነት በሁሉም በኩል ዋጋ አስከፍሏል፥ ይህ መደገም የለበትም ብለዋል።

የሃገር ሽማግሌዎቹ "ዳግም በዊልቸር የሚገፉ ሰዎች እንዲፈጠሩ አንፈልግም፣ ዳግም እግራቸው አጥተው የሚያነክሱ ወጣቶች እንዲኖሩ አንሻም፣ ዳግም አይናቸው አጥተው በሰው የሚመሩ ሰዎች እንዲፈጠሩ አንፈልግም" ብለዋል።

ከሃገር ሽማግሌዎቹ እና የሃይማኖት አባቶቹ ጋር በነበረ ውይይት ሀሳብ የሰጡት የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ በበኩላቸው፥ በትግራይ በኩል የሚጀመር ጦርነት በፍፁም አይኖርም ሲሉ ለሽማግሌዎቹ ተናግረዋል።ጀነራል ታደሰ ወረደ "በእኔ [የስልጣን] ወቅት በትግራይ ጦርነት አይኖርም። ለጦርነት የሚደረግ ዝግጅት የለም" ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪ ጀነራል ታደሰ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ለተፈናቃዮች ጥያቄ ምላሽ በሚሰጥ እንዲሁም የትግራይ ዳግመ ግንባታ አጀንዳዎች ዙርያ እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ ፌደራዊ መንግሥትና በሕግ በታገደዉ ህወሓት መካከል የተፈጠረዉ ጠብ ወደ ጦርነት እንዳያመራ ለመማፀን ወደ መቀሌ ከተጓዙ የሐገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት መሪዎች በከፊልምስል፦ Million Haileselassie/DW

ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማትየተወከሉ ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት መሪዎች ከሁለት ሳምንት በፊት በመቐለ በመገኘት በተመሳሳይ አጀንዳ ከግዚያዊ አስተዳደሩ እና ህወሓት መሪዎች ጋር መወያየታቸው የሚታወስ ሲሆን ከዛ ቀጥሎም ከትግራይ ወደ አዲስአበባ የተጓዙ የትግራይ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አሕመድ ጋር በፅሕፈት ቤታቸው መወያየታቸው ይታወሳል። እነዚህ ትላንት መቐለ የደረሱ የሰላም ልኡካን፥ ትላንት ከህወሓት መሪዎች ጋር በህወሓት ፅሕፈት ቤት ዛሬ ደግሞ በትግራይ ከሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በሰላም ጉዳይ ተወያይተዋል።

ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ

ነጋሽ መሐመድ

ታምራት ዲንሳ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW