1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጉባኤ ዉሳኔ

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 15 2013

የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባደረገዉ ሥብሰባዉ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን የቦርድ ኃላፊንና የአባላትን ሹመት አፅደቀ። ምክር ቤቱ የመገናኛ ብዙሐን ረቂቅ አዋጅንና የፀረ ሙስና ኮሚሽንን ዳግም ለማደራጀት የተረቀቀዉን ደንብ ለየሚመለከታቸዉ ኮሚቴዎች መርቷል።

Äthiopien Addis Ababa | Parlament diskutiert Anti-Hassrede und Missinformationsgesetz
ምስል፦ DW/Y. Gebrezihaber

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጉባኤ ዉሳኔ

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባደረገዉ ሥብሰባዉ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን የቦርድ ኃላፊንና የአባላትን ሹመት አፅደቀ። ምክር ቤቱ የመገናኛ ብዙሐን ረቂቅ አዋጅንና የፀረ ሙስና ኮሚሽንን ዳግም ለማደራጀት የተረቀቀዉን ደንብ ለየሚመለከታቸዉ ኮሚቴዎች መርቷል። ምክር ቤቱ የተለያዩ ውሳኔዎችን ያሳለፈበትን ሥብሰባ በይፋ ያደረገዉ ርዕሡ ባልታወቀ ጉዳይ ላይ ለአንድ ሰዓት ያሕል በዝግ ከመከረ በኋላ ነው። ጋዜጠኞችና ለምክር ቤቱ አባላት ገለፃና ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጋበዙ ባለ ሥልጣናት ከጉባኤዉ አዳራሽ ውጪ ለመቆየት ተገድደዋል። የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW