1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሕዝብ እና ቤት ቆጠራ መራዘም

ሐሙስ፣ መጋቢት 19 2011

የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የሕዝብና ቤት ቆጠራ መራዘሙን ተቃወመ። የትግራይ ክልል ውሳኔው የመንግሥት የማስፈፀም አቅሙ ደካማ መሆኑ ያሳያል ብሎታል። የሕዝብና ቤት ቆጠራ ኮሚሽን የተላለፈበትን ምክንያት ይፋ ባደረገው መግለጫ፣ በግጭቶች ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ወደየነበሩበት ሳይመለሱ ቆጠራውን ማካሄድ እንደማይቻል ማመልከቱ ይታወሳል።

Äthiopien Stadtansicht Mekele
ምስል DW/M. Hailessilasie

የትግራይ ክልል መራዘሙን ተቃውሟል

This browser does not support the audio element.

በተደጋጋሚ እየተራዘመ መካሄድ ከነበረበት ግዜ ሁለት ዓመት ያለፈው የሕዝብና ቤት ቆጠራ በያዝነው ወር መጋቢት 29 ሊካሄድ ዕቅድ ወጥቶለት በዝግጅት ሂደት ላይ ከቆየ በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት ላልተወሰነ ግዜ እንዲተላለፍ የውሳኔ ሀሳብ ቀርቧል።  በጉዳዩ ላይ የተለያዩ አስተያየቶች እየቀረቡ ሲሆን የትግራይ ክልል መንግሥት የአስፈፃሚውን አካል ውሳኔ ተቃውሞታል። የሕዝብና ቤት ቆጠራን አስመልክቶ የተላለፈውን የውሳኔ ሀሳብ መግለጫ የሰጡት የትግራይ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድርና የንግድ፣ ኢንዳስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ሐላፊ ዶክተር አብረሃም ተኸስተ ቆጠራው አለመካሄዱ የመንግሥትን የማስፈፀም አቅም ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው ብለዋል። እንዲሁም በሂደቱም የግልፅነት ችግር መኖሩን አክለው ገልፀዋል።በትግራይ ክልል በኩል ግን ቆጠራውን ለማካሄድ ሙሉ ዝግጁነት መኖሩን ዶክተር አብርሃም ተኸስተ ተናግረዋል፡፡ ይህን አስመልክቶ የሚመለከታቸው የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW