1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሕዳሴ ግድብ፣ መገናኛ ዘዴዎችና የባለሙያ አስተያየት

ገበያው ንጉሤ
ረቡዕ፣ ጳጉሜን 5 2017

ሁሉም የዓለማችን ትልልቅ የቴሌቪሽንና የህትመት ሜዲያዎች የግድቡን ግንባታና መጠን በማድነቅ፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአካባቢው አገሮች ጭምር የኃይል ምንጭ የመሆን አቅም ያለው መሆኑን በመግለጽና ከሁሉም በላይ ግን ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገት ትልቅ እመርታ የሚፈጥር መሆኑን በሰፊው ገልጸዋል

ኢትዮጵያ በበኒ ሻንጉል-ጉሙዝ ክልል በአባይ ወንዝ ላይ ያስገነባችዉ የሕዳሴ ግድብ በከፊል።ግድቡ ትናንት መመረቁን ዓለም አቀፍ መገናኛ ዘዴዎች በሰፊዉ ሲዘግቡ ነበር
ኢትዮጵያ በበኒ ሻንጉል-ጉሙዝ ክልል በአባይ ወንዝ ላይ ያስገነባችዉ የሕዳሴ ግድብ በከፊል።ግድቡ ትናንት መመረቁን ዓለም አቀፍ መገናኛ ዘዴዎች በሰፊዉ ሲዘግቡ ነበርምስል፦ Office of the Prime Minister-Ethiopia

የሕዳሴ ግድብ፣ መገናኛ ዘዴዎችና የባለሙያ አስተያየት

This browser does not support the audio element.


ትናንት የተመረቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብየዓለም የምመገናኛ ብዙኃንን ትኩረት እስከዛሬም ድረስ እንደሳበ ነው። ሁሉም የዓለማችን ትልልቅ የቴሌቪሽንና  የህትመት ሜዲያዎች የግድቡን ግንባታና መጠን በማድነቅ፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአካባቢው አገሮች ጭምር የሀይል ምንጭ የመሆን አቅም ያለው መሆኑን በመግለጽና ከሁሉም በላይ ግን ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እድገት ትልቅ እመርታ የሚፈጥር መሆኑን በሰፊው ገልጸዋል። ጋዜጦቹና መገናኛ ብዙኃኑ የታችኛው ተፋሰሥ አገሮች በተለይም ግብጽ ግን በግድቡ ግንባታ፤ የውኃ አሞላልና አስተዳደር ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ያላት በመሆኑ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው አለመግባባት  ሊቀጥልና ሊያድግ እንደሚችልም ያላቸውን ስጋት አንስተዋል።
 

ግድቡ ታሪክ ለዋጭ ነው ስለመባሉ

ኢትዮጵያ ግን ከዚህ ግድብ መገንባትና ወደሥራ መግብት በጎላ ሌላ ምራፍ ውስጥ የምትገባ መሆኑንን በርክታ ባለሙያዎችም እየተናገሩ ነው። ደቡብ አፍርካ የሚገኘው የሴኩሪቲ ጥናት ተቋም ያፍርካ ቀንድ ተመራማሪ የሆኑት ሚስተር ሞሴስ ክሪስፐስ ኦኬሎ ግድቡን ታሪክ ለዋጭ ብለውታል።
 

ጥራትና ደረጃውን በሚመለክት የባለሙያ አስተያየት

ዲደብሊው የውኃ ሀብት መሀንዲስና የህዳሴው ግድብየባለሙያዎች አማካሪ ቡድን አባል የሆኑትን ዶክተር ጥሩ ሰው አሰፋን ስለዚህ ብዙ እየተነገረለት  ስላለው የህዳሴ ግድብ ግንባታ፤ ጥራትና ደረጃ ተጨማሪ አስተያየት ጠይቆ ነበር። እሳቸው እንደሚሉት ግድቡ በዘመናዊ ቴክኖሎጂና ያለማቀፍ ባለሙያዎች  የሰጧቸው አስተያየቶችም ተካተው የተሰራ በመሆኑ እስካሁን ካዩአቸው ግድቦች የተለየ ነው ።
 

የሕዳሴ ግድብ ትናንት በተመረቀበት ወቅት ከቀረቡት ትርዒቶች አንዱ።የግድቡ መመረቅ የዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን ትኩረት ሥቧል።ምስል፦ Luis Tato/AFP/Getty Images

ግብጽ በዚሁ ግድቡ በተመረቀበት ዕለት ጭምር ተቃውሞ ማሰማቷንና ለመንግስታቱ ድርጅት አቤት ማለቷን በማስታወስም፤ ኢትዮጵያ  ወደ ታችኛው ተፋሰስ አገሮች የሚፈሰው ውሀ ሳይቀንስ ግድቡን መሙላት መቻሏ የግብጽን ጩኸት ሊቀንሰው ባይችልም ሰሚ አታገኝም`` በማለትም ለሁሉም የሚያዋጣው በመተባበር መስራትና መጠቀም መሆኑን አስታውሰዋል።

ገበያው ንጉሴ

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ሥለሺ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW