1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመቀሌው የእግር ኳስ ግጭት

ሰኞ፣ ግንቦት 7 2009

ቅዳሜ ዕለት በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ስቴዲየም በመቀሌ ከነማ እና በባህርዳር ከነማ የእግር ኳስ ቡድን የተካሄደው የብሔራዊ ሊግ መደበኛ ግጥሚያ በተፈጠረ ግጭት ተቋርጧል። ጨዋታው ዛሬ ጠዋት በድጋሚ ይካሄዳል ተብሎ ቢጠበቅም ሳይካሄድ ቀርቷል።

Äthiopien Stadt Mekelle
ምስል DW/Y. Gebreegziabher

Fussball fans Streit in Mekelle follow up - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

ከትናንት በስትያ በመቀሌ  ዩኒቨርስቲ ስቴዲየም ግጭት የተቀሰቀሰው ግጥሚያው በመካሄድ ላይ እያለ እንደነበር የአይን እማኞች ለዶይቸ ቬለ ገልጸዋል። የአይን እማኞቹ ግጭቱን ለማስቆም ጣልቃ የገባው ፖሊስ አስለቃሽ ጪስ መተኮሱን እና ተመልካቾችም መደብደባቸውን ገልጸውልናል። በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የቆሰሉ ሰዎችን የሚያሳዩ ምስሎች ይታያሉ። 
 ቅዳሜ ዕለት በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ስቴዲየም ሥለተፈጠረዉ ግጭት የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን ምላሽ እንዲሰጠን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር መንግሥት አረጋዊን በሥልክ ለማነጋገር ሞክረን  ነበር። ኮማንደር አረጋዊ ግን ዶይቸ ቬለ «በሠላም ጊዜ አልመጣም» በማለት ሥለግጭቱ መናገር አልፈለጉም። 
የግጭቱን መንስኤ ለማወቅ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባለሥልጣናትንም ለማነጋገር ሞክረናል። ይሁንና ፌዴሬሽኑ የቅዳሜውን ግጥሚያ አስመልክቶ ዝርዝር ዘገባ እየጠበቀ እንደሆነ ነው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ወንድምኩን አላየው የገለፁልን። እሳቸውም ጨዋታው ዛሬ ጠዋት በድጋሚ ይካሄዳል ተብሎ ቢጠበቅም ሳይካሄድ መቅረቱን ገልጸውልናል።
ልደት አበበ
ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW