1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የመብት ጥሰትን የመከላከል ጥረት በደቡባዊ ኢትዮጵያ ክልሎች

ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ቅዳሜ፣ ሰኔ 21 2017

የኢትዮጵያ የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም በዜጎች ላይ የሚከሰቱ የመብት ጥሰቶችን የመከላከልና የማረም ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ ፡፡ተቋሙ ከመልካም አስተዳደር እጦት ጋር ተያይዘው ለሚነሱ አቤቱታዎች በቅንጅት ምላሽ ለመስጠት ያስችለኛል ያለውን የመግባቢያ ሥምምነት ከሦስት ክልላዊ መንግሥታት ጋር በሀዋሳ ተፈራርሟል ፡፡

Äthiopien | Aro Aseres Gizaw, Ombudsstelle gegen Menschenrechtsverletzungen
ምስል፦ Shewangizaw Wegayehu/DW

የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚያደርገው የመብት ማስከበር ጥረት

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ከመልካም አስተዳደር ጋር ተያይዘው በዜጎች ላይ የሚከሰት የመብት ጥሰትን በጋራ ለመከላከልና ለማረም ያስችለኛል ያለውን ሥምምነት ከሦስት ክልላዊ መንግሥታት ጋር ትናንት በሀዋሳ ተፈራርሟል፡፡ ተቋሙ ሥምምነቱን ያካሄደው ከሲዳማ ፣ ከማዕከላዊ እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥታት ጋር ነው ፡፡ ስምምነቱ የደሞዝ እና የይዞታ መፈናቀልን ጨምሮ በክልሎቹ የሚስተዋሉ የመብት ጥሰት አቤቱታዎች ላይ በቅንጅት ለመሥራት እንደሚያስችል የተቋሙ ሃላፊዎች ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል፡፡

በወላይታ ዞን የመምህራን ደሞዝ አሁንም አልተከፈለም ፤ ትምህርትም አልተጀመረም

በክልሎቹ የሚስተዋሉ የመብት ጥሰቶች ምን አይነት ናቸው ?

አቶ አስረስ ግዛው በኢትዮጵያ የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም የሀዋሳ ቅርንጫ ጽህፈት ቤት ተጠባባቂ ሃላፊ ናቸው ፡፡ አቶ አስረስ እንደሚሉት በሦስቱ ክልሎች በየዓመቱ የመብት ጥሰት ተፈጸመብን ያሚሉ  በርካታ ዜጎች ለተቋሙ አቤቱታቸውን ያቀርባሉ ፡፡ አቤት ባዮች ይዘው የሚቀርቡት ጉዳይ የተለያየ መሆኑን የጠቀሱት ተጠባባቂ ሃላፊው “ ከእነኝህም መካከል የደሞዝ አለመከፈል ፣ ከተከፈለም ያለሠራተኞች ይሁንታ መቁረጥ ፣ እንዲሁም ከይዞታ መፈናቀልና ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ አቤቱታዎች ይገኙበታል ፡፡ ይህ ሥምምነት እነኝህን አቤቱታዎች ከክልል መንግሥታት ጋር ተቀራርቦ ለመፍታት ያስችላል “ ብለዋል ፡፡

አቤት ባዮች ይዘው የሚቀርቡት ጉዳይ የተለያየ መሆኑን የጠቀሱት ተጠባባቂ ሃላፊው “ ከእነኝህም መካከል የደሞዝ አለመከፈል ፣ ከተከፈለም ያለሠራተኞች ይሁንታ መቁረጥ ፣ እንዲሁም ከይዞታ መፈናቀልና ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ አቤቱታዎች ይገኙበታል ፡፡ ምስል፦ Shewangizaw Wegayehu/DW

የመብት ጥሰትና የተወካዮች ም/ቤት ቋሚ ኮሚቴ ዉሳኔ 

የመብት ጥሰቶች በትምህርቱ ዘርፍ ላይ

በደቡብና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ከደሞዝ ክፍያ አለመፈጸም ጋር በተያያዘ በርካታ አቤቱታዎች   ሲቀርቡ፣ ዶቼ ቬሌም በተደጋጋሚ ቅሬታዎቹን ሲዘግብ ቆይቷል፡፡ በተለይም የመብት ጥሰቱ ጎልቶ በሚታይበት በትምህርት ዘርፉ ላይ የተወሰነ መሻሻል መኖሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት አማኑኤል ጳውሎስ ይናገራሉ ፡፡ ነገር ግን አሁንም ያልተፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች መኖራቸውን ለዶቼ ቬለ አስተያታቸውን የሰጡት የማህበሩ ፕሬዝዳንት “ በ2017 ዓ.ም መምህራን ሙሉ ደሞዝ የማግኘት ሁኔታ መሻሻል አሳይቷል ፡፡ ነገር ግን አሁንም በርካታ የመልካም አስተዳደር ጉድለቶች ይስተዋላሉ ፡፡ አንዳንድ ቦታ ላይ ከፍቃዱ ውጭ ደሞዝን የመቁረጥ ፣ የትምህርት ማሻሻያ  የሚፈቅደውን ክፍያ አለመፈጸም ፣ ከፍላጎት ወጭ ዝውውር ማድረግ ይጠቀሳሉ “ ብለዋል ፡፡

ኢትዮጵያ የመብት ጥሰት እንድታቆም መጠየቁ

የሥምምነቱ ተስፋ

የኢትዮጵያ የህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ከክልሎቹ ጋር ያደረገው ስምምንት በጎ እርምጃ መሆኑን የተናገሩት የማህበሩ ፕሬዝዳንት “ በሥምምነቱ መሠረት መሥራት ከተቻለ ለመምህራንም ሆኑ ሌሎች ሠራተኞች ላይ ለሚደርሱ የመብት ጥሰቶችን ለመከላከል ያስችላል ፡፡ ተፈጽመው ሲገኙም በፍጥነት ለማረም ያስችላል የሚል ተስፋ አለኝ ፡፡ በተለይም አብዛኛው ጥሰት የሚፈጸመው በወረዳ መዋቅሮች ላይ  ነው ፡፡ የተቋሙ እና የክልል መንገሥታቱ ተቀራርቦ መሥራት እስከ ታችኛው የአስተዳደር መዋቅሮች በመውረድ ጥሰቶችን በቅንጅት ለመፍታት ዕድል ይፈጥራል “ ብለዋል ፡፡

ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ታምራት ዲንሳ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW