1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመን ከአሊ አብደላ ሳሌሕ በኋላ

ማክሰኞ፣ ኅዳር 26 2010

የቀድሞው የየመን ፕሬዝዳንት አሊ አብደላ ሳሌሕ ሞት አገሪቱን ከመንታ መንገድ ላይ ጥሏታል። ለአራት አስርት አመታት በየመን ፖለቲካ ላይ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ሳሌሕ አምባገነን እና በየጊዜው ጠላት እና ወዳጆቻቸውን የሚቀያይሩ ቢሆኑም እንኳ ሞታቸው በየርስ በርስ ጦርነት ለተዘፈቀችው የመን መርዶ ሆኗል።

Jemen Ali Abdullah Saleh, Muammar al-Gaddafi und Hosni Mubarak
ምስል Reuters/A. Waguih

ሳሌሕ በሑቲ አማፅያን የተገደሉት ባለፈው ሰኞ ነበር

This browser does not support the audio element.

የቀድሞው የየመን ፕሬዝዳንት አሊ አብደላ ሳሌሕ ሞት አገሪቱን ከመንታ መንገድ ላይ ጥሏታል። ለአራት አስርት አመታት በየመን ፖለቲካ ላይ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ሳሌሕ አምባገነን እና በየጊዜው ጠላት እና ወዳጆቻቸውን የሚቀያይሩ ቢሆኑም እንኳ ሞታቸው በየርስ በርስ ጦርነት ለተዘፈቀችው የመን መርዶ ሆኗል። ከሞታቸው ሶስት ቀናት በፊት የሶስት አመታት አጋራቸውን ሑቲዎች ፊት ነስተው ከሳዑዲ የሻከረ ወዳጅነታቸውን ለማደስ ዳር ዳር እያሉ ነበር። እንደ ተንታኞች አባባል ግን "ቁማራቸው" አልሰራም። የሑቲዎቹ መሪ አብድል ማሊክ አል-ሑቲ የቀድሞው የየመን ፕሬዝዳንት የተገደሉት በአገር "ክሕደት" ተወንጅለው መሆኑን ተናግረዋል። የመን የሚገኘው ግሩም ተክለኃይማኖት እንደሚለው የሳሌሕ ሞት ከተሰማ በኋላ ሰንዓ ሐዘን ተጭኗታል። ለመሆኑ የአሊ አብደላ ሳሌሕ ሞት በየመን የርስ በርስ ጦርነት ላይ ምን ትርጉም አለው? 
ግሩም ተክለኃይማኖት
እሸቴ በቀለ
ነጋሽ መሐመድ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW