1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

መኢአድ በሰሞኑ የመንግሥት እርምጃ ላይ

ዓርብ፣ ኅዳር 7 2011

መኢአድ ዛሬ በጽህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ መንግሥት ሰሞኑን በሙስናና እና በሰብዓዊ መብት ጥሰት ጠርጥሮ የያዛቸውን የቀድሞ ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ለህግ ማቅረብ መጀመሩ ተጠናክሮ መቀጠል አለበትም ብሏል። ለመንግስት እርምጃ ተግባራዊነትም የአፍሪቃ ህብረት እና የተመድ እንዲሁም ጎረቤት ሀገራትም እገዛ እንዲያደርጉ ጠይቋል።

Logo Äthiopien Opposition Partei AEUP

የመኢአድ መግለጫ

This browser does not support the audio element.

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ መንግሥት መውሰድ የጀመረው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ እርምጃ በጎ ጅምር ነው ሲል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ አወደሰ። መኢአድ ዛሬ በጽህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ መንግሥት ሰሞኑን በሙስናና እና በሰብዓዊ መብት ጥሰት ጠርጥሮ የያዛቸውን የቀድሞ ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ለህግ ማቅረብ መጀመሩ ተጠናክሮ መቀጠል አለበትም ብሏል። ለመንግስት እርምጃ ተግባራዊነትም የአፍሪቃ ህብረት እና የተመድ እንዲሁም ጎረቤት ሀገራትም እገዛ እንዲያደርጉ ጠይቋል። በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ድርጅቱ በተለያዩ አካባቢዎች ስላካሄዳቸው እንቅስቃሴዎች እና ስለ ከፈታቸው አዳዲስ ቢሮዎችም ገለጻ አድርጓል። መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ወኪላችን ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።  


ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW