የመካሕ አደጋና ሐጂ
ሐሙስ፣ መስከረም 6 2008ማስታወቂያ
ባለፈዉ ሳምንት በመካዉ አል-ሐራም መስጊድ ላይ ግዙፍ ክሬን በመዉደቁ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸዉና መቁሰላቸዉ በዘንድሮዉ የሐጂ ጉዞ ላይ ያሳረፈዉ ተፅዕኖ ብዙም ያለ አይመስልም።ባለፈዉ ሳምንት በደረሰዉ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር አንድ መቶ አስራ-ስምንት ደርሷል።በመቶ የሚቆጠሩ ቆስለዋል።ለሐጂ የሚደረገዉ ጉዞና ፀሎት ግን አልታጎለም።በየዓመቱ እንደሚሆነዉ ሁሉ ኢትዮጵያዉያንን ጨምሮ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የተለያዩ ሐገራት ሙስሊሞች ሳዑዲ አረቢያ ገብተዋል።ጉዞዉን የታዘበዉ ነብዩ ሲራክን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ነብዩ ሲራክ
ነጋሽ መሐመድ
ሒሩት መለሠ