የመገናኛ ዘዴዎች ትርዒት በበርሊን
ዓርብ፣ ነሐሴ 27 2003ማስታወቂያ
በርሊን ዉስጥ በየዓመቱ ለመተልካች የሚቀርበዉ የኤሌክትሪኒክስ መገናኛ ዘዴዎች ትርዒት የዘንድሮዉ ዛሬ በይፋ ተከፍቷል።ለአራት ቀናት በሕዝብ በሚጎበኘዉ በዚሕ ትርዒት ላይ ከቀረቡት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች መካካል በተንቀሳቃሽ ሥልክ፥ በቴሌቪዥንና በኮምፒዉተር መሳሪያዎች ላይ የተደረገዉ ለዉጥና የታየዉ ዕድገት የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ሐይለ ሚካኤል እንዳለዉ ብዙዉን ተመልካች የማረከ ነዉ።በትርዒቱ ላይ ከአንድ ሺሕ በላይ ኩባንዮች አዳዲስ ምርቶቻቸዉን አቅርበዋል።ይልማን በስልክ አነጋግሬዉ ነበር።
ይልማ ሐይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ