የሙስሊሞች መዋቅራዊ ሽግግር ኮሚቴ መግለጫ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 17 2011ማስታወቂያ
በመጪው ሚያዝያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም ዑላማዎች፤ ምሁራን እና የሀገር ሽማግሌዎች የሚሳተፉበት ጉባኤ እንደሚጠራ የሙስሊሞች መዋቅራዊ ሽግግር ኮሚቴ ዐስታወቀ። የኮሚቴው አመራር አባላት ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እስካሁን በኮሚቴው የተሠሩ ሦስት ዐበይት ጉዳዮች በጉባኤው እንደሚጸድቁ እና በባለአደራ አመራር አማካኝነት የመጅሊስ ምርጫ እንደሚካሄድ ተናግረዋል። በጉባኤው ከሦስት መቶ በላይ ተሳታፊዎች እንደሚገኙ ተገልጧል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ነጋሽ መሐመድ
ተስፋለም ወልደየስ