1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

«የሚመጣዉን ለመቀበል ዝግጁ ነኝ» ልደቱ አያሌዉ

ነጋሽ መሐመድ
ረቡዕ፣ ግንቦት 2 2015

የኢትዮጵያ መንግስት ለሕክምና ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኙትን አቶ ልደቱ አያሌዉን ጨምሮ 11 ሰዎችን «የሽብር ፕሮፓጋንዳ በመንዛት፣ የክልልና የፌደራል መንግስትን በኃይል ለመጣል በማሴር ወንጅሏቸዋል

Äthiopien Addis Abeba | Lidetu Ayalew, äthiopischer Politiker
ምስል፦ privat

«ሥርዓቱን መጋፈጥ የማንችል ከሆነ ማን ለዕዉነት ሊቆም ይችላል» አቶ ልደቱ

This browser does not support the audio element.

እዉቁ የኢትዮጵያ መንግስት ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌዉ በቅርቡ መንግስት ያወጀባቸዉን የአሸባሪነት ክስ በአካል ተገኝተዉ ለመሟገት መወሰናቸዉን አስታወቁ።የኢትዮጵያ መንግስት ለሕክምና ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኙትን አቶ ልደቱ አያሌዉን ጨምሮ 11 ሰዎችን «የሽብር ፕሮፓጋንዳ በመንዛት፣ የክልልና የፌደራል መንግስትን በኃይል ለመጣል በማሴር ወንጅሏቸዋል። የኢትዮጵያ የፀጥታና ደሕንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ባለፈዉ ሚያዚያ 22 ባወጣዉ መግለጫዉ «የሽብር ኃይሎች» ያላቸዉን ሰዎች ለመያዝና ኢትዮጵያ ዉስጥ ለፍርድ  ለማቅረብ ተጠርጣሪዎቹ ከሚኖሩባቸዉ ሐገራት የፀጥታ ኃይሎችና ከከዓለም የፖሊስ ድርጅት (ኢንተር ፖል) በጋራ እየሰራ መሆኑን አስታዉቋል።አቶ ልደቱ እንዳሉት ግን ራሳቸዉ ሔደዉ ክሱን ለመጋፈጥ ወስነዋል።ከአቶ ልደቱ ጋር ያደርግነዉን ሙሉ ቃለ መጠይቅ ያድምጡ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW