1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የማሊ ወቅታዊ ሁኔታ

ዓርብ፣ ሐምሌ 20 2004

ማሊን ከገባችበት ቀውስ ለማውጣት እቅድ አውጤቻለሁ የሚለው የማሊ የሽግግር መንግስት ከሃገሪቱ ዋነኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃወሞ ገጥሞታል ። መንግሥት የአመራር ብቃት ይጎድለዋል ሲሉ የተቹት እነዚሁ ፓርቲዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሥልጣን እንዲወርዱ ትናንት ጠይቀዋል ።

epa03176925 Mali coup leader Captain Amadou Sanogo (L) stands next to Malian parliamentary speaker, Dioncounda Traore (R), after holding talks at the junta headquarters in Kati, outside of Bamako, Mali 09 April 2012. Reports state that Captain Sanogo has signed an accord agreeing to return Mali to constitutional rule. Malian parliamentary speaker, Dioncounda Traore, is set to act as interim president and lead a transitional administration until elections. EPA/TANYA BINDRA
ምስል picture-alliance/dpa

ማሊን ከገባችበት ቀውስ ለማውጣት እቅድ አውጤቻለሁ የሚለው የማሊ የሽግግር መንግስት ከሃገሪቱ ዋነኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃወሞ ገጥሞታል ። መንግሥት የአመራር ብቃት ይጎድለዋል ሲሉ የተቹት እነዚሁ ፓርቲዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሥልጣን እንዲወርዱ ትናንት ጠይቀዋል ። በሌላ በኩል ፓሪስ ፈረንሳይ ሲታከሙ የቆዩት የማሊ የሽግግር መንግሥት ፕሬዝዳንት ዲዮንኩንዳ ትራኦሬ ዛሬ ማምሻውን ወደሃገራቸው ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል ። በጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ ሞዲቦ ዲያራ የሚመራው የማሊ የሽግግር መንግሥት ከተመሰረተ ገና 3 ወሩ ነው ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዲያራ እስከ መጪው ማክሰኞ ማለትም ሐምሌ 24 ፣ 2004 ዓም ድረስ ብሔራዊ የአንድነት መንግሥት እንዲመሰርቱ የምዕራብ አፍሪቃ የምጣኔ ሃብት ማህበረሰብ በምህፃሩ ኤኮዋስ አዟል ። የሚመሰረተው መንግሥትም ከ 4 ወራት በፊት ሰሜናዊ ማሊን ከተቆጣጠረው አክራሪ ሙስሊም ኃይል ጋር አንድ አይነት ስምምነት ላይ እንዲደርስ የአካባቢው ሸምጋይ ሃገራት ጠይቀዋል ። ይሁንና ይህ ሃላፊነት የተሰጣቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዲያራ ሥልጣን እንዲለቁ የማሊ ዋና ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪል ማህበራት ጠይቀዋል ።

Mali Flüchtlingeምስል picture alliance/abaca

ከነዚህም አንዱ በእንግሊዘኛው ምህፃር FDR በመባልየሚጠራውየተባበሩት የሪፐብሊኩ ና የዲሞክራሲ መከላከያ ግንባሩ ነው ግንባሩ ባወጣው መግለጫ በዲያራ የሚመራው የማሊ የሽግግር መንግሥት የአመራርብቃት የለውም ሃገሪቱም የሽግግሩ መንግሥት ከተቋቋመ አንስቶ የኃሊት እየሄደች ነው በማለት ጠቅላይሚኒስትሩ ከሥልጣን እንዲወርዱ ጠይቋል። ሆኖም የማሊን ሁኔታ በቅርበትየሚከታተሉ ወገኖች ይህ ጥያቄ የተነሳበትወቅትተገቢአ ይደለምይላሉ ። ከነዚህም አንዱ የ Inter-African Union of Human Rights በምህፃሩ IUHR ወይም አፍሪቃ አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ፕሬዝዳንት ባሂማ ኮኔ ናቸው ።

« ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሽግግሩ ወቅት ይችን ሃገር ሊመሩ የሚችሉ ሰዎች በአጠገባቸው ቢኖሩ ኖሮ በዚህ ቀውጢ ሰዓት መንግሥት ሥልጣኑን እንዲለቅ የተጠየቀበትን ሁኔታ ማሟላቱ ባልገደደም ነበር ። በሰሜን የሃገሪቱ ክፍል የደረሰውን ቀውስ ማስወገድ የሚቻልበትን ሠላማዊ መፍትሄ ለማስገኘትን ምርጫን ለማደራጀትም በተቻለ ነበር ። ይሄን የሚያደርግ ቡድን ነበረ የሚያስፈልገን ። »

Mali Flüchtlingeምስል picture alliance/abaca

ኮኔ የተቃወሙትን ሃሳብ ያቀረበው FDR ዲያራን የሚተቸው በአክራሪ ሙስሊሞች የተያዘውን ሰሜን ማሊን በጦርነትም ይሁን በድርድር ለማስለቀቅ አንዳችም ስልት አልቀየሱም ሲል ነው ። ግንባሩ ማሊን ከመፈንቅለ መንግሥቱ በኋላ ከገባችበት ቀውስ ያወጣል ሲል የሽግግር መንግሥቱ የቀየሰውን የሰላም እቅድም ራዕይ አልባ ነው ያለው እጅግ አንገብጋቢና ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባ ብሔራዊ ጉዳዮችን እምብዛም አላካተተም ብሏል ግንባሩ ። በነዚህ ምክንያቶችም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሥልጣን ይውረዱ እያለ ነው ። ይሁንና የአፍሪቃ አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅት ፕሬዝዳንት ባሂማ ኮኔ በዚህ አይስማሙም በርሳቸው አስተያየት የሽግግሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን መልቀቅ ጉዳት እንጂ ጥቅም የለውም ። ይህን ጥያቄ የሚያቀርቡ ወገኖችም በቅድሚያ የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት ይገባቸዋል ።

«የሽግግሩ መንግሥት ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከሥልጣን ቢያነሱ እርምጃው ሃገሪቱን ወደ ባሰ ቀውስ ውስጥ ነው የሚከታት ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥልጣን እንዲለቁ የሚጠይቁ ሁሉ በመጀመሪያ የቤት ሥራቸውን መሥራት ይኖርባቸዋል ። ሃገሪቱም በስተመጨረሻ ከገባችበት ማጥ ማውጣት መቻል ይኖርባቸዋል »

ምስል Reuters

በርግጥም የሽግግሩ መንግሥት ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ አክራሪ ሙስሊሞች በሰሜን ማሊ ይዞታቸውን እያጠናከሩ ነው የሄዱት ። ምትክ የሌላቸውንም የዓለም ቅርሶችም አውድመዋል ። በሰሜን ማሊ መያዝ ሰበብ 400 ሺህ ማሊዎች ተፈናቅለዋል ። የማሊ የሽግግር መንግሥት ዋነኛ ሃላፊነት ለሰሜን ማሊ ቀውስ መፍትሄ መሻት የነበረ ቢሆንም በዚህ ረገድ አንዳች የፈየደው ነገር የለም ። የሽግግሩ መንግሥት ብሔራዊ የአንድነት መንግሥት እንዲመሰርት ሸምጋዩ የምዕራብ አፍሪቃ የምጣኔ ሃብት ማህበረሰብ አዟል ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲወርዱ ስለ ለተነሳው ጥያቄ የሸምጋዮቹ አንድ ምንጭ በሰጡት መልስ ይህ በማሊዎች ነው የሚወሰነው ብለዋል ። የማሊው የሽግግር ጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን እንዲለቁ የሚጠይቀው የተባበሩትየሪፐብሊኩናየዲሞክራሲመከላከያግንባርካካተታቸው ፓርቲዎች ውስጥ የሽግግሩ መንግሥት ፕሬዝዳንት የዲዮንኩንዳ ትራኦሬ የማሊ ዲሞክራሲያዊ ህብረት ፓርቲ ይገኝበታል ። በምርጫ ሥልጣን የያዙትን የቀድሞ የማሊ ፕሬዝዳንት አማዱ ቱማኒ ቱሬን በመጋቢት ወር በመፈንቅለ መንግሥት ክሥልጣን ያስወገዱት ዲያኮንዳ ትራኦሬ ከሁለት ወራት የፓሪስ ፈረንሳይ ህክምናቸው በኋላ ዛሪ ወደ ሃገራቸው ይመለሳሉ ። ቱሬ ባለፈው ግንቦት የሽግግሩ መንግሥት በይፋ ስራውን በሚጀምርበት ዋዜማ ላይ ነበር በቢሮአቸው ውስጥ በተነሳ አመፅ ከተጎዱ በኋላ ፈረንሳይ ለህክምና የሄዱት ።

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW