የሜርክል ስኬቶች
ማክሰኞ፣ መጋቢት 4 2010ማስታወቂያ
የጀርመን ምክር ቤት ምርጫ ከተካሄደ ከአምስት ወር አጋማሽ በኋላ እህትማማቾቹ የክርስቲያን ዴሞክራት ህብረት እና የክርስቲያን ሶሻል ህብረት ፓርቲ ከሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ ጋር ተጣምረው መንግሥት ለመመስረት የደረሱበትን ስምምነት ትናንት በፊርማቸው አጽድቀዋል። የክርስቲያን ዴሞክራቶች ህብረት ፓርቲ ሊቀመንበር ወይዘሮ አንጌላ ሜርክል ጀርመንን ለአራተኛ የሥልጣን ዘመን ለመምራት ነገ ቃለ መሀላ ይፈጽማሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ሜርክል ላለፉት 12 ዓመታት በሥልጣን ላይ መቆየቱ እና ለተጨማሪ አራት ዓመታት መሪ ሆኖ መቀጠሉ እንዴት ተሳካላቸው? የአሁኑ የመንግሥት ምሥረታ ረዥም ጊዜ መውሰድ በሀገር ውስጥም ሆኖ በአውሮጳ በነበራቸው ተሰሚነታቸው ላይ ተጽእኖ ይኖረው ይሆን? የተጣማሪው የሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ ይዞታስ እንዴት ይታያል። የዛሬው አውሮጳ እና ጀርመን ዝግጅታችን ትኩረት ነው። የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለ ሚካኤል አዘጋጅቶታል።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ