የሜርክል ኦባማ ዉይይትና የጀርመን አሜሪካ ግንኙነት
ሰኞ፣ ሰኔ 22 2001ማስታወቂያ
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ ሥልጣን ከያዙ ወዲሕ ካንዴም-ሁለቴ ጀርመንን ጎብኝተዋል።ከጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት ከአንጌላ ሜርክል ጋር ቢያንስ አራቴ ተወያይተዋል። የኦባማ የመጨረሻ ጉብኝት-ዉይይት ወር ሳይደፍን የጀርመንዋ መራሒተ መንግሥት ዋሽግተን ደርሰዉ ተመለሱ።ቅዳሜ።ጤና ይስጥልኝ እንደምን ዋላችሁ።የሁለቱ መሪዎች የድግግሞሽ ጉብኝት-ዉይይት ምክንያት መነሻች፤ የአለም አንደኛና ሰወስተኛ ሐብታም ሐገራት የወዳጅነት ዳራ ማጣቀሻ፤ እንድምታዉ መድረሻችን ነዉ ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
dw,
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ