1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የምሥራቅ ኢትዮጵያ የፀጥታ ውይይት መድረክ

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 25 2011

በምሥራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች በየጊዜው በሚነሳው ግጭት ሳቢያ በሰው ህይወትና ንብረት ላይ የሚደርስ ጉዳትም ሆነ የዜጎች መፈናቀል አልቆመም፡፡ በአካባቢው ባለው ሕገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የሚዘዋወረው ሕገወጥ መሳርያ እና ሕገወጥ ገንዘብም ለአካባበቢው ሰላም መደፍረስ ተግዳሮትነቱ እንደቀጠለ ነው።

Äthiopien Konferenz des Sicherheitschefs in Dire Dawa
ምስል DW/M. Teklu

የምስራቅ ኢትዮጵያ የፀጥታ ውይይት መድረክ

This browser does not support the audio element.

በምሥራቅ የአገሪቱ አካባቢዎች ዛሬም ድረስ ስር ነቀል መፍትሄ አግኝቶ መብረድ ያልቻለውን ግችት ማቆም እና ችግሩን መፍታት ያልተቻለበትን ምክንያት ምንነት ጠለቅ ብሎ ለመመርመር ትናንት በድሬደዋ የተካሄደው የምሥራቅ ኢትዮጵያ  አጎራባች ክልሎች የፀጥታ ውይይት መድረክ  በርካታ  ሀሳቦች ተነስተውበታል ፡፡በየጊዜው የአካባቢውን የፀጥታ ሥራ በዕቅድ ለመምራት ጥረት ቢደረግም ወደ አፈፃፀም ሲሸጋገር ችግሮች ማጋጠማቸው በመድረኩ ተነስቷል ፡፡  የሀገር መከላከያ ምሥራቅ ዕዝና የፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች የፀጥታ እቅዱን ተግባራዊ ከማድረግ ጎን ለጎን ተጠያቂ የሚያደርግ አሰራር አለመኖሩ ዋና ችግር መሆኑን አንስተዋል ፡፡በዚህም አመራሩ ሀላፊነት ወስዶ መስረት ከራሱ መጀመር እንዳለበት ነው የጠቆሙት ፡፡በየአካባቢው እየተነሱ ያሉ ግጭቶችንና አሁን ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በጥልቀት የመረመረው የውይይቱ መድረክ ዋነኛ ያለውን የተጠያቂነት አሰራር አለመኖር ችግር ለመቅረፍ የሚረዳ በየደረጃው የዕቅድ አፈፇፀምን ለመገምገምና ተጠያቂነት ማስፈን የሚያስችል አዲስ የአሰራር ስርዓት አስቀምጧል ፡፡ለዚህም ኮሚቴዎችን አዋቅሯል፡፡የመከላከያ ዕዝ ከፍተኛ አዛዦች፣ የፌደራል ፖሊስና የክልል የፀጥታ ሃላፊዎች የተገኙበት ይህ መድረክ ያስቀመጠው አሰራር በአካባቢዎቹ ግጭትን በማስቆም ፣ የዜጎች መፈናቀልን በማስቀረት፣ ሕገወጥ የየንግድ እንቅስቃሴውን በማስቆም እና የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ በማደራጀት ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን  አዲስ ተስፋ ተጥሎበታል ፡፡  

መሳይ ተክሉ

አርያም ተክሌ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW