የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪክ ማኅበራት ስለምርጫው ውጤት
ሰኞ፣ ሐምሌ 5 2013ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ተደጋግሞ ተራዝሞ ሰኔ አጋማሽ የተካሄደው የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብሔራዊ ምርጫ አሸናፊ ብልጽግና ፓርቲ መሆኑን አስታውቋል። ስለውጤቱ ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው የፓለቲካ ፓርቲዎችና እና የሲቪል ማኅበር አመራሮች ከጠበቁት ተቃራኒ እንደሆነባቸው ገልፀዋል።"ጥምር መንግሥት መመሥረት የሚያስችል የምርጫ ውጤት ይኖራል የሚል ግምት ነበረን" ያሉም አሉ።የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ "ተዓማኒ የሆና ምርጫ ለአገራችን ዜጎች ሰጥተናል" ብለዋል። የውጤት ማሳወቂያው ዕለት ባደረጉት ንግግር።የቦርዱ ገለልተኝነት ላይ ያላቸውን ምልከታ የተጠየቁት አስተያየት ሰጪዎቹ ቦርዱ ሥራውን በገለልተኝነት ያስፈፀመ ነውና ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ