1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን መግለጫ

ረቡዕ፣ ጥቅምት 25 2013

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በተልዕኮ ላይ እያለ ትናንት ዕኩለ ሌሊት ላይ በትግራይ ልዩ ኃይል የደረሰበት ጥቃት «ከባዕድ ወረራ የከፋ የከሃዲነት ርምጃ ነው» ሲሉ ክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ

Stellvertretender Premierminister von Äthiopien - Demeke Mekonnen Hassen
ምስል፦ G. Tiruneh

ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በተልዕኮ ላይ እያለ ትናንት ዕኩለ ሌሊት ላይ በትግራይ ልዩ ኃይል የደረሰበት ጥቃት «ከባዕድ ወረራ የከፋ የከሃዲነት ርምጃ ነው» ሲሉ ክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በሰጡት መግለጫ በዛሬው ዕለት ልዩ ኃይሉን በማንቀሳቀስ በአማራ ሕዝብ ላይ ወረራ ለማካሄድ ከፍተኛ ርብርብ በማካሄድ ላይ ይገኛል ብለዋል።  ለዚሁ ወቅታዊ ጉዳይ ሲባል አዲስ የተቋቋመው የተግባቦት ኮሚቴ ቃል አቀባይ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን «ግጭቱ በአንድ ቤተሰብ መሀከል የሚደረግ መኾኑ ቢያሳዝንም ህግ የማስከበር ሥራ የግድ ነው» ብለዋል። «ይኼ ግጭት በትግራይ ሕዝብ እና በተቀረው የኢትዮጵያ ሕብዝ መካከል አይደለም» ሲሉም አክለዋል።  ትግራይ ውስጥ የኢንተርኔት እና የስልክ አገልግሎት በመቋረጡ ከትግራይ በኩል አስተያየት ለማካተት አልቻልንም። ሰለሞን ሙጬ ዝርዝር ዘገባ አለው።

ሰለሞን ሙጬ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW