1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሩስያ የዩክሬን ወረራና የኔቶና የአውሮጳ ኅብረት ምላሽ  

ሐሙስ፣ የካቲት 17 2014

ከሩስያ ጋር ተፋጦ የቆየው የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ቃል ኪዳን ድርጅት በምህጻሩ ኔቶ«ሆን ተብሎ፣ለረዥም ጊዜ የታቀደና ግልጽ»ያለውን የሩስያ ወረራው አውግዟል።የሩስያ በበኩሏ በዩክሬን የጀመረችው ዘመቻ ግቦች ወታደራዊ ክምችትን ማስወገድ እና ሀገሪቱን ከአፍቃሪ ናዚዎች ነጻ ማድረግ ነው ብላለች።

Ukraine Konflikt | Russischer Militärangriff
ምስል Efrem Lukatsky/AP Photo/picture alliance

የሩስያ የዩክሬን ወረራና የኔቶና የአውሮጳ ኅብረት ምላሽ

This browser does not support the audio element.

ሩስያ ዛሬ የዩክሬንን ድንበር ጥሳ በመግባት በተለያየ አቅጣጫ ሙሉ ጥቃት ሰንዝራለች። በዩክሬን ዋና ከተማ ኪቭና በሌሎች ከተሞችም የሚሳይል ጥቃቶች እንደተፈጸማባት ዩክሬን አስታውቃለች። በጥቃቱ ወታደራዊ እዞች፣ የኪቭ ቦሪስፒል አየር ማረፊያና በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ህንጻዎች ዒላማ ሆነዋልም ባላለች ዩክሬን ።ወራራውን በምድርና በባህር  ያካሄደችው ሩስያ በበኩልዋ የዩክሬን ጦር መሳሪያውን እንዲያስቀምጥ ጠይቃለች። ከሩስያ ጋር ተፋጦ የቆየው የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ቃል ኪዳን ድርጅት በምህጻሩ ኔቶ  «ሆን ተብሎ፣ለረዥም ጊዜ የታቀደና ግልጽ» ያለውን የሩስያ ወረራው አውግዟል።  የመከላከያ እቅዶቹን ስራ ላይ መዋል መጀመሩን የተናገረው ኔቶ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ተጨማሪ ኃይሎችን ለማሰማራት ለጦር አዛዦቹ ተጨማሪ ስልጣን መስጠቱንም አስታውቋል። ሩስያ በበኩሏ በዩክሬን የጀመረችው ዘመቻ ግቦች ወታደራዊ  ክምችትን ማስወገድ እና ሀገሪቱን ከአፍቃሪ ናዚዎች ነጻ ማድረግ ነው ብላለች። በጉዳዩ ላይ ከብራሰልሱን ወኪላችን ጋር የተደረገውን ቃለ መጠይቅ ለማዳመጥ ከታች የሚገኘውን የድምፅ ማዕቀፍ ይጫኑ።

ምስል AP Photo/picture alliance


ገበያው ንጉሴ


ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW