የርዋንዳ የጦር ወንጀለኞች እና የተበየናቸው የዕድሜ ልክ እስራት ቅጣት10 ታኅሣሥ 2001ዓርብ፣ ታኅሣሥ 10 2001በአሩሻ ታንዛንያ የሚገኘው የተመ የርዋንዳን የዘር ማጥፋት ወንጀል ጉዳይን የሚመለከተዉ የጦር ወንጀል ችሎት ከሁለት ቀናት በፊት በቀድሞዉ ወታደራዊ ጀነራል ቴዎኔስቴ ቦጎሶራና በሶስት የቀድሞ ወታደራዊ መኮንኖች ላይ የዕድሜ ልክ እስራት ፈረደ።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግየቀድሞ ወታደራዊ ጀነራል ቴዎኔስቴ ቦጎሶራናምስል APማስታወቂያየቀድሞዎቹ የሩዋንዳ ወታደራዊ ባለስልጣናት በሀገሪቱ እአአ በ 1994 ዓም በቱትሲዎችና በለዘብተኛ ሁቱዎች አንጻር የተፈፀመዉን የዘር ማጥፋት ወንጀል በማቀነባበር የተከሰሱ ሲሆን፡ ካለፉት አስራ አንድ ዓመታት ወዲህ በእስራት ላይ የሚገኙት ቦጎሶራ ባቀነባበሩት ጭፍጨፋ በዚያን ጊዜ ወደ ስምንት መቶ ሺህ ሰው ነበር የተገደሉት።