1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሮሂንግያ ሙስሊሞች

ረቡዕ፣ ጳጉሜን 1 2009

በሁለት ሳምንት ውስጥም ከ400 በላይ ሰዎች ተገድለዋል። ህጻናት እና ሴቶች የሚያመዝኑባቸው 125 ሺህ የሚሆኑ ስደተኞች በአስቸጋሪ ሁኔታ ድንበe አቋርጠው ባንግላዴሽ ገብተዋል።

Bangladesch Massenflucht der Rohingyas
ምስል picture-alliance/dpa/B. Armangue

የሮሂንግያ ሙስሊሞች

This browser does not support the audio element.

በምያንማር የሮሂንግያ ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ በተከፈተው ግጭት ምክንያት ህዝቡ ለሞት እና ለስደት ተዳርጓል። ከ 2 ሳምንት በፊት አማጽያን በ አንድ የፖሊስ ጣቢያ ላይ ባደረሱት ጥቃት ሰበብ  የማይንማር ወታደሮች በህዝቡ ላይ ጦርነት ከፍተው ጥቃት እያደረሱ መሆኑ እየተዘገበ ነው። በሁለት ሳምንት ውስጥም ከ400 በላይ ሰዎች ተገድለዋል። ህጻናት እና ሴቶች የሚያመዝኑባቸው 125 ሺህ የሚሆኑ ስደተኞች በአስቸጋሪ ሁኔታ ድንበe አቋርጠው ባንግላዴሽ ገብተዋል። በሮሂንግያ ሙስሊሞች ላይ ይሄ ሁሉ በደል የሚፈጸመው የኖቤል የሰላም ተሸላሚ አውን ሳን ሱቺ ሥልጣን ላይ ባሉበት ጊዜ መሆኑ ማነጋገሩ ቀጥሏል።  ገበያው ንጉሴ ዘገባ አዘጋጅቷል

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW