የሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ የተመሠረተበትን 25ኛ ዓመት፤
ዓርብ፣ መስከረም 27 2009ማስታወቂያ
የሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ የተመሠረተበትን 25ኛ ዓመት በሀገሪቱ ያለዉን ሁኔታ በመገንዘብ በሀዘን እያሳለፈ እንደሚገኝ ተገለጠ። ሀገር ዉስጥ ካለፉት ከስምንት ወራት በላይ የተባባሰዉ የሕዝብ ቁጣና ብሶት ድርጅቱ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን የሚከታተልበት መንገድም እንዲለወጥ ግድ እንዳለዉ አስታዉቋል። የሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ የ25ኛ ኢዮቤልዩ በዓሉን ሀገር ዉስጥ ስላለዉ ሁኔታ ስጋቱን በመግለፅ እንዲሁም የሚታየዉን የሰብዓዊ መብት ይዞታ የሚቃኝ፤ ብሎም የመፍትሄ ሃሳብ የሚያቀርብ የመወያያ መድረክ በማዘጋጀት እንደሚያሳልፈዉ አመልክቷል። ዘጋቢያችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ከአዲስ አበባ ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ