የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር መታሰር
ዓርብ፣ ጳጉሜን 4 2008ማስታወቂያ
የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ይድነቃቸዉ ከበደ በደኅንነት ኃይሎች ታሰሩ። አቶ ይድነቃቸዉ ከበደ ባለፈዉ ሳምንት ከተቃጠለዉ የቂሊንጦ ማረምያ ቤት የታሰሩ ታራሚዎች ተብሎ የተለጠፈዉን የስም ዝርዝር እያነበቡ ሳለ በሁለት ሲቢል ለባሽ የደኅንነት ኃይሎች መወሰዳቸዉንና ዛሬ በፍርድ ቤት ቀርበዉ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ እንደተጠየቀባቸዉ ፓርቲዉ መግለፁን የአዲስ አበባዉ ወኪላችን የላከልን ዘገባ ያመልክታል።
ዮኃንስ ገብረ እግዚአብሔር
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ