1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ

ረቡዕ፣ ሰኔ 28 2009

የኢትዮጵያ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መሻሻል በማሳየቱ ለአደጋ የተጋለጡ የዓለም ቅርሶች ከሰፈሩበት መዝገብ ላይ መነሳቱ ተዘገበ።

Bildergalerie Rote Liste des gefährdeten Welterbes (Nationalpark Simien)
ምስል picture alliance/Robert Harding

Ber. AA (Semen National Park) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መሻሻል በማሳየቱ ለአደጋ የተጋለጡ የዓለም ቅርሶች ከሰፈሩበት መዝገብ ላይ መነሳቱ ተዘገበ። ፓርኩ ከአደጋ ነጻ እንደሆነ የገለጠው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት በእንግሊዝኛ ምህፃሩ (UNESCO) ነው። ፓርክ ከመጠን በላይ በግጦሽ በመጎዳቱ እንዲሁም  ዋሊያ አይቤክስ፣ የሰሜን ቀይ ቀበሮ እና ሌሎች ግዙፍ አጥቢ እንስሳት ቊጥራቸው በመመናመኑ ነበር ለአደጋ የተጋለጡ የዓለም ቅርሶች መዝገብ ላይ ሰፍሮ የቆየው። የዩኔስኮ ውሳኔ የብዝኃ-ሕይወት ጥበቃው እንዲጠናከር፤ የአገር ጎብኚዎች ፍሰት እንዲቀጥል ትልቅ አስተዋጽዖ ይኖረዋል ሲሉ የፓርኩ ኃላፊ ተናግረዋል። 

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ኂሩት መለሰ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW