የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 9 2014![Bahir Dar | Binnenflüchtlinge aus Waghemra](https://static.dw.com/image/59551520_800.webp)
ማስታወቂያ
ሰሞኑን በደቡብ ወሎ ዞን አንዳንድ አካባቢዎች በአዲስ በተቀሰቀሰው ጦርነት ብቻ ከ250 ሺህ በላይ ወገኖች መፈናቀላቸውን በአማራ ክልል የደቡብ ወሎ ዞን አስታወቀ። አጠቃላይ በጦርነቱ የተፈናቀሉት ከ1 ነጥብ 7 ሚሊዮን መብለጡን ክልሉ አመልክቷል። በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ደግሞ የመሰረታዊ ሸቀጦች እጥረት ነዋሪዎችን ለርሀብ ዳርጓል ተብሏል። በጦርነት ቀጣና ያሉ ከ4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ወገኖች ዓለም አቀፉ ረጂ ድርጅት አስካሁን መድረስ እንዳልቻለም ባለስልጣናቱ አመልክተዋል፡፡
ዓለምነው መኮንን
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ