1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሰበታ ተፈናቃዮች ምሬት 

ሰኞ፣ መጋቢት 9 2011

እነዚሁ ከ4 ወር በፊት ቤታቸው የፈረሰባቸው ሰዎች ከ3 ሺህ በላይ መሆናቸውን በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ ጽህፈት ቤት በሰጡት መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ቤታቸው በመፍረሱ በአብያተ ክርስቲያን ተጠልለው እንደሚገኙ የተናገሩት እነዚሁ ሰዎች የሚበሉት እና የሚጠጡት እንደሌላቸው የልጆቻቸውም ትምሕርት መስተጓጓሉን በምሬት ገልጸዋል።

Karte Äthiopien englisch

«ቤት የፈረሰባቸው ሰዎች ከ3 ሺህ በላይ ይሆናሉ»

This browser does not support the audio element.

ሰበታ ውስጥ ወለቴ ቀበሌ 03 ይገኙ የነበሩ መኖሪያ ቤቶቻቸው ህገ ወጥ ተብሎ በመፍረሱ ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን አስታወቁ። እነዚሁ ከ4 ወር በፊት ቤታቸው የፈረሰባቸው ሰዎች ከ3 ሺህ በላይ መሆናቸውን በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ ጽህፈት ቤት በሰጡት መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ቤታቸው በመፍረሱ በአብያተ ክርስቲያን ተጠልለው እንደሚገኙ የተናገሩት እነዚሁ ሰዎች የሚበሉት እና የሚጠጡት እንደሌላቸው የልጆቻቸውም ትምሕርት መስተጓጓሉን በምሬት ገልጸዋል። መንግሥት እኛን ህገ ወጥ እያለ በህገ ወጥ መንገድ ሊያስተናግደን አይገባም የሚሉት እነዚሁ ተፈናቃዮች አፋጣኝ መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ጠይቀዋል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW