የሰባት ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግለጫ
ሐሙስ፣ ሐምሌ 18 2011ማስታወቂያ
ተቃዋሚውን የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድን ጨምሮ ግንባር ለመፍጠር በሂደት ላይ ያሉ 7 ተቃዋሚ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያተኮረ መግለጫ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ሰጥተዋል። ፓርቲዎቹ በመግለጫቸው ከሰኔ 15፣2011 ዱ ግድያ በኋላ እየተፈጸመ ነው ያሉት የጅምላ እሥራት ማስፈራራት በአስቸኳይ እንዲቆም ጠይቀዋል።በአማራ ክልል የታሰሩ ንጹሀን ያሏቸው ዜጎች ጉዳያቸው ተጣርቶ ከእስር እንዲለቀቁም አሳስበዋል።የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት ባልደራስ አባላት እና ደጋፊዎች ላይ ደረሰ ያሉት መዋከብ እንዲቆምም ጥሪ አቅርበዋል።መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ሰሎሞን ሙጬ ዝርዝሩን አዘጋጅቷል።