1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብት ጥሰት በአማራ ክልል

እሑድ፣ ኅዳር 2 2016

ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ግጭቶች እና ጦርነቶች እየተደጋገሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችም ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ እየተባባሱ መምጣታቸው በተደጋጋሚ ተዘግቧል ። ጦርነቱ በቀጠለበት የአማራ ክልል የሰብአዊ መብት ጥሰቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱም ይነገራል ። ሙሉውን ውይይት ከድምፅ ማእቀፉ ማድመጥ ይቻላል።

ታሪካዊቱ የላሊበላ ከተማ
ታሪካዊቱ የላሊበላ ከተማ ውስጥ ጦር መሣሪያ ያነገበ ታጣቂምስል Solan Kolli/AFP/Getty Images

ከምንም በላይ ሕጻናት፤ ሴቶችና አረጋውያን ተጎጂዎች ናቸው

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያውስጥ በተለይ ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ግጭቶች እና ጦርነቶች እየተደጋገሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችም ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ እየተባባሱ መምጣታቸው በተደጋጋሚ ተዘግቧል ። በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ጦርነት በቀጠለበት የአማራ ክልል የሰብአዊ መብት ጥሰቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱም ይነገራል ።

ሰሞኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባወጣው መግለጫ፦ በአማራ ክልል ድሮንን ጨምሮ በከባድ ጦር መሣሪያዎች በተሰነዘሩ ጥቃቶችበሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱን እንዲሁም 200 ሴቶች መደፈራቸውን ገልጿል ። ኢሰመኮ፦ በድሮን ጥቃት «የአንድ ዓመት ከሰባት ወር ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች እንደተገደሉ እና የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው» መገለጹ የሰብአዊ መብት ጥሰት ጥልቀቱን የሚያሳይ ነው ሲሉ በርካቶች ሥጋታቸውን ገልጸዋል ።

መግለጫውን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት «ትክክለኛ መረጃ ላይ ያልተመሰረተና ሚዛናዊነት የጎደለው ነው» ሲል ውድቅ አድርጎታል ። ለመሆኑ ጦርነቱ በቀጠለበት በአማራ ክልል የሰብአዊ መብቶች አያያዝ እና ጥሰቱ ምን ይመስላል? የዛሬው የእንወያይ መሰናዶዋችን የሚያተኩርበት ነጥብ ነው ። 

በዚህ ውይይት ተሳታፊ እንዲሆኑ ለመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) እንዲሁም ለመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ በዶይቸ ቬለ በኩል የላክነው የኢሜል ግብዣም ሆነ የስልክ ጥሪ ውይይቱን እስካደረግንበት ጊዜ ድረስ ምላሽ አላገኘም ። ሦስት ተወያዮች ሐሳባቸውን የሚያቀርቡበት ሙሉውን ውይይት ከድምፅ ማእቀፉ ማድመጥ ይቻላል ።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW