1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሱማሊያ ስደተኞችን ለመመለስ የገንዘብ ማሰባሰብ

ሐሙስ፣ ጥቅምት 11 2008

የሱማሊያ ስደተኞችን ከጎረቤት ኬንያ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እና ለማቋቋም የሚያስችል የገንዘብ ርዳታ ለማሰባሰብ ቤልጂየም ብራስልስ ውስጥ ረቡዕ፣ ጥቅምት 10 ቀን፣ 2008 ዓም በተጠራ የለጋሾች ስብሰባ ከ105 ሚሊዮን ዩሮ በላይ መገኘቱ ተገልጧል። ስደተኞቹ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱት በፍቃዳቸው እንደሚሆንም የተመድ አስታውቋል።

Kenia Dadaab, Somalische Flüchtlinge
ምስል Getty Images

[No title]

This browser does not support the audio element.

የለጋሾችን ስብሰባ የጠራው የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን በእንግሊዝኛ ምኅፃሩ (UNHCR) ከአውሮጳ ኅብረት ጋር በመተባበር መሆኑ ተዘግቧል። በዚህ የሱማሊያ ስደተኞችን ወደሀገራቸው መመለስን እና ማቋቋምን በተመለከተው ስብሰባ የአውሮጳ ኅብረት የውጭ ጉዳይ ኃላፊ እና የሶማሊያ ጠቅላይ ሚንስትርን ጨምሮ ከ40 የሚበልጡ ሃገራት ተወካዮች ተገኝተዋል። የብራስልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሤስብሰባውን ተከታትሎ የሚከተለውን ዘገባ አጠናቅሮልናል።

ገበያው ንጉሤ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW