1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሱዳን ከአሜሪካን የሽብርተኝነት መዝገብ መውጣት

ረቡዕ፣ ጥቅምት 11 2013

ዩናይትድ ስቴትስ አሸባሪዎችን የሚደግፉ ሃገራት ናቸው ከምትላቸው ዝርዝር ውስጥ እንደምታስወጣት አስታውቃለች። የሱዳን የሽግግር መንግሥት የተጠየቀውን ከፍሎ ከአሸባሪዎች ዝርዝር ለመውጣት ዝግጁነቱን አመልክቷል። ከሱዳን ሌላ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ የአሸባሪዎች ዝርዝር ውስጥ ኢራን እና ሰሜን ኮርያ ይገኛሉ።

Sudan Khartum US-Außenminister Pompeo und Abdalla Hamdok
ምስል፦ Sudanese Government/Saudi Press Agency/picture-alliance

«ሱዳን የተጠየቀችውን ካሣ መክፈል ይኖርባታል»

This browser does not support the audio element.

ዩናይትድ ስቴትስ አሸባሪዎችን የሚደግፉ ሃገራት ናቸው ከምትላቸው ዝርዝር ውስጥ እንደምታስወጣት አስታውቃለች። ዋሽንግተን ኻርቱምን ከዚህ ዝርዝር ውስጥ ለማውጣት በጎርጎሪዮሳዊው 1998 በኬንያ እና ታንዛኒያ ዋና ከተሞች በሚገኙ ኤምባሲዎቿ ላይ አልቃይዳ ላደረሰው የቦምብ ጥቃት ከ300 ሚሊየን ዶላር በላይ ካሣ እንድትከፍል ጠይቃለች። የሱዳን የሽግግር መንግሥት የተጠየቀውን ከፍሎ ከአሸባሪዎች ዝርዝር ለመውጣት ዝግጁነቱን አመልክቷል። ከሱዳን ሌላ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ የአሸባሪዎች ዝርዝር ውስጥ ኢራን እና ሰሜን ኮርያ ይገኛሉ። ከብራስልስ ገበያው ንጉሤ ዝርዝሩን ልኮልናል።

ገበያው ንጉሤ

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW