1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሱዳን የርስበርስ ጦርነት እንዲቆም የሚደረገዉ ግፊትና ጫና

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 9 2017

ከሁለት አመታት በላይ የዘለቀውን በሱዳን የቀጠለውን ደም አፋሳሽ ግጭት ለማስቆምና ህዝቡ ሰብአዊ እርዳታ የሚያገኝበትን ሁኔታ መፍትሄ ለመሻት የ17 አገራት ተወካዩችና አምስት መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዎች በጉባኤው ላይ ተሳትፈዋል።

«ህዝብ የሚያጫርሰውን ደም አፋሳሹ ህፃናትን እናቶችን አእና አቅመ ደካሞችን ተፈጀውን የርስ በርስ ጦርነት በእንዲህ ሁኔታ ማየት ተገቢ አይደለም» የብሪታንያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ዴቪድ ላሚ
የሱዳን ጉዳይ ጉባኤ በለንደን።ከሁለት አመታት በላይ የዘለቀውን አፋሳሽ ግጭት ለማስቆምና ህዝቡ ሰብአዊ እርዳታ የሚያገኝበትን ሁኔታ ለመሻት  የ17 አገራት ተወካዩችና አምስት መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዎች በጉባኤው ላይ ተሳትፈዋል።ምስል፦ Isabel Infantes/WPA Pool/Getty Images

የሱዳን የርስበርስ ጦርነት እንዲቆም የሚደረገዉ ግፊትና ጫና

This browser does not support the audio element.

 

የሱዳን የርስበርስ ጦርነት አሁንም ለሶስተኛ ዓመት እንደቀጠለ ነዉ።ጦርነቱ በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ሕዝብ ፈጅቷል።ከ13 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ አሰድዷል ወይም አፈናቅሏል።ሱዳን ዉስጥ አስቸኳይ ሰብአዊ ርዳታ የሚፈልገዉ ሕዝብ ቁጥር ከ20 ሚሊዮን በልጧል።ተፋላሚ ኃይላት ጦርነቱን በድርድር እንዲያቆሙ የተለያዩ ወገኖች ቢጠይቁም እስካሁን ግን ጥያቄ፣ግፊትና ጫናዉ ተቀባይነት ያገኘ አይምስልም።በያዝነዉ ሳምንት ለንደን ዉስጥ ተሰብስበዉ የነበሩት የተለያዩ ሐገራትና የርዳታ ድርጅቶች ተጠሪዎች ግን ጦርነቱ እንዲቆም በድጋሚ ጠይቀዋል።

ከሁለት አመታት በላይ የዘለቀውን በሱዳን የቀጠለውን ደም አፋሳሽ ግጭት ለማስቆምና ህዝቡ ሰብአዊ እርዳታ የሚያገኝበትን ሁኔታ መፍትሄ ለመሻት  የ17 አገራት ተወካዩችና አምስት መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅት ተወካዎች በጉባኤው ላይ ተሳትፈዋል። ጉባኤውን የመሩት የብሪታኒያ የውጭ ገዳይ ሚኒስትር ሲሆኑ የጀርመን መንግስትን በመወከል ደግሞ የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር አናሊና ባይቡርክ ተገኝተዋል።የብሪታንያዉ የውጭጉዳይ ሚንስትር ዴቪድ ላሚ ባደረጉት ንግግር ይህ እልቂት ያለ ማቋረጥ መቀጠሉ እጅግ የሚያሳዝን እና ተገቢም እንዳልሆነ ገልፀዋል።

ሁላችሁንም በጉባኤው ተሳታፊነት መፍትሄ ከመሻት በመምጣታችሁ ምስጋናዪን አቀርባለሁ።እንግዲህ ሁለት አመት ሙሉ ምንም መፍትሄ ያልተገኘለት  ህዝብጠየሚያጫርሰውን ደም አፋሳሹ ህፃናትን እናቶችን አእና አቅመ ደካሞችን ተፈጀውን የርስ በርስ ጦርነት በእንዲህ ሁኔታ ማየት ተገቢ አይደለም፣ አሁን መፍትሄ ለመፈለግ እዚህ ተገናኝተናል ሀላችንም በጋራ ማድረግ የሚገባንን ነገር አድርገን ይሄ ጦርነት በአፋጣኝ መቆም አለበት

 የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር  አናሊና ባይቡከርም ከ ዴቪድ ላሚ በመቀጠል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል የተከበሩ። አቶ ዴቪድ የተከበራችሁ ተሳታፊ ሚንስትሮች እዚህ ቦታ ላይ ስለተሰበሰብን አመሰግናለሁ። ዛሬ አንድ ምነግራችሁ ታሪክ አለ አንድ በህመም ሆስፒታል ውስጥ ስለተሰቃየ ልጅ በጦርነቱ ምክኒያ ሙሉ ህክምና ማግኘት ሳይችል ቀርቶ የሞተ ነው

የሱዳን መከላከያ ጦርና የሐገሪቱ ፈጥኖ ደራሽ ጦር የገጠሙት ጦርነት እንደ ግሪጎሪያኑ አቆጣጠር ባለፈዉ ሚያዚያ 15 2025 ሁለተኛ ዓመቱን ደፍኗል። ምስል፦ AFP

ለናቱ ምን አላት ሆዴን አሞኛል እናቴ ቶሎ ድኜ ውጭ ወጥቸ መጫወት እችላለሁ ከጓሰኞቼ ጋር ነበር ያላት ከጥቂት ደቂቃዎች በውሀላ ግን ህይወቱ አልፏል። ይህ ቨአሁኑ ሰአት በብዙ የሱዳን ቤተሰቦችና የሱዳን ልጆች እናቶች አቅመደካሞች ላይ እየደረሰ ያለ ችግር ነው

ዚህ ችግር ተሯሩጠን መፍትሄ መፈለግ የሁላችንም ሀላፊነት ነው።ዴቪድ ላሚ አያይዘው ያለውን ችግር ሲገልፁእዚህጋ ትልቁ እንቅፋት የእርዳታ ማነስ ወይም ደግሞ የረጅዎች አለመሳተፍ አይደለምዋናው ትልቁ እንቅፋት አሁን የ ፖለቲካ ፈቃደኝነት ነው።

መኮንን ሚካኤል

ነጋሽ መሐመድ

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW