1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሱዳኖች ድርድርና ዉጤቱ

ሐሙስ፣ መስከረም 10 2005

የሁለቱ ሱዳኖች ልዩነት ብዙ ነዉ።የድንበር ግዛት ይገባኛል፥ የነዳጅ ዘይት ሐብት፥ አንዱ የሌላዉን ተቃዋሚ ወይም አማፂ ቡድን መርዳት፥ የዜግነት--- እያለ አንዱ ሲነካ ሌላዉ አብሮ የሚመዘዝ ብዙ እና ዉጥንቅጥም ነዉ።

South Sudan’s chief negotiator, Pagan Amum (L) sits alongside Sudan’s Defence Minister Abdel-Rahim Mohamed Hussein (C), Sudanese spokesman Omer Dahab (R) as they announce that both countries have agreed to improve ties and cease hostilities during the latest round of talks in Addis Ababa on July 7, 2012. Sudan and South Sudan pledged to cease hostilities along their disputed oil-rich border Saturday but stopped short of actually signing an agreement, officials said. The verbal agreement came as the latest round of talks closed in the Ethiopian capital ahead of celebrations Monday to mark one year of independence for South Sudan.Negotiations resumed in May following weeks of deadly clashes along the oil-rich disputed border in April which brought the two rivals back to the brink of all-out war. The United Nations passed a resolution in May urging both sides to resolve outstanding disputes on oil sharing revenue and border demarcation by August 2. AFP PHOTO/JENNY VAUGHAN (Photo credit should read JENNY VAUGHAN/AFP/GettyImages)
ተደራዳሪዎችምስል Getty Images/AFP
አል በሽርምስል Reuters


በጠብ የሚፈላለጉት የሰሜን እና የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንቶች የፊታችን ዕሁድ አዲስ አበባ ዉስጥ ፊት ለፊት ተገናኝተዉ ለመነጋገር ቀጠሮ ይዘዋል።ሁለቱ ፕሬዝዳቶች ፊትለፊት ለመነጋገር መፍቀዳቸዉ ጦር ያማዘዘዉን ልዩነት ለማጥበብ በተከታታይ የተደረገዉ ድርድር አግባቢ ደረጃ የመድረሱ ምልክት ተደርጎ ነዉ የታየዉ።የድርድሩን ሒደት የሚከታተሉ ዲፕሎማቶች እንዳስታወቁትም ተደራዳሪዎች በተለይ የድንበር መካለልን እና የነዳጅ ዘይት ሐብት ክፍፍልን በተመለከተ ከተጠበቀዉ በላይ ተቀራርበዋል።ያም ሆኖ አሁንም በሁለቱ ወገኖች መሐል ሙሉ መተማመን አይታይም።

ባለፈዉ ሚያዚያ ያዋጋቸዉ የሁለቱ ሱዳኖች ልዩነት ብዙ ነዉ።የድንበር ግዛት ይገባኛል፥ የነዳጅ ዘይት ሐብት፥ አንዱ የሌላዉን ተቃዋሚ ወይም አማፂ ቡድን መርዳት፥ የዜግነት--- እያለ አንዱ ሲነካ ሌላዉ አብሮ የሚመዘዝ ብዙ እና ዉጥንቅጥም ነዉ።ሱዳኖች ዉጥንቅጡን ጠብ እንዲያስወግዱ የአፍሪቃ ሕብረት ከመሸምገል፥ ምዕራባዉያን ከማስጠንቀቅ፥ የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት ቀን ከመቁረጥ አልቦዘኑም።

አዲስ አበባ ላይ የተያዘዉን ድርድርን የሚከታተሉ ዲፕሎማቶች ካለፈዉ ማክሰኞ ጀምሮ እንዳስታወቁት ግን ተደራዳዊዎች ሌላዉ ቢቀር ድንበር መካካለልንና የነዳጅ ዘይት ሐብት ክፍፍልን በሚመለከት እስከዚሕ ሳምንት ድረስ የያዙትን የተራራቀ አቋም ወደ ማቀራረቡ አዘንብለዋል።



ዛሬ ደግሞ የሁለቱ ሐገራት መሪዎች የፊታችን ዕሁድ አዲስ አበባ ዉስጥ ፊት ለፊት ተገናኝተዉ ለመነጋገር መወሰናቸዉ ተሰምቷል።የፀጥታ ጥናት ተቋም-ISS በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ የፖለቲካ ጉዳይ ተንታኝ ዶክተር ጂዲ ማርቲንስ ኦኬኬ እንደሚሉት ሁለቱ ፕሬዝዳንቶች ፊትለፊት ለመነጋገር መወሰናቸዉ እጅግ የተወሳሰበዉን ልዩነት ለማጥበብ በጣም ጠቃሚ እርምጃ ነዉ።

«የሁለቱ ፕሬዝዳንቶች መገናኘት በጣም ጠቃሚ ነዉ።በተለይ ሁለቱን ሐገራት በጣም የሚያወዛግበዉን የድንበር ችግርን ለማቃለል በጣም ይጠቅማል።የድበሩ ዉዝግብ የተካረረዉ አወዛጋቢዉ ግዛት ነዳጅ ዘይት የሚመረትባቸዉን አንዳድ አካባቢዎችን የሚያካትት በመሆኑ ነዉ።»

ከአወዛጋቢዎቹ አካባቢዎች ደቡብ ሱዳን ነፃነትዋን ስታዉጅ በይደር የተተወዉ የአብዬ ግዛት አንዱ ምናልባትም ትልቁ ነዉ።እስካሁን በተደረገዉ ድርድር ድንበርን በማካለሉ ረገድ መግባባት የተደረሰበት ግዛት የትነት፥ የማካለሉ ሒደት እንዴትነት ላሁኑ በሚስጥር እንደተያዘ ነዉ።

የደቡብ ሱዳን የገንዘብ ሚንስትር ኮስቲ ማኒቢ ንጋዪ እንዳስታወቁት ግን ፕሬዝዳት ዑመር ሐሰን አል-በሽርና ፕሬዝዳት ሳል ቫኪር በመጪዉ ዕሁድ አዲስ አበባ ዉስጥ የሚያደርጉት ዉይይት ሁለቱን ሐገራት ከሁነኛ ዉል ማድረሱ አይቀርም።

ዉሉ ከተፈረመ ደግሞ ሚንስትሩ እንደሚሉት ደቡብ ሱዳን ምርትና ሽያጩን በማቆሟ የሁለቱንም ሱዳኖች በጣሙን የራስዋን የደቡብ ሱዳንን ካዝና ወና ያስቀረዉ ነዳጅ ዘይት ለሽያጭ ዳግም ይቀዳል።

«የአፍሪቃ ሕብረት አደራዳሪዎች አዲስ በቆረጡት ጊዜ መሠረት ስምምነቱን ለመፈረም መስከረም ሃያ-ሰወስት የመጨረሻ ስብሰባ ይደረጋል።ይሕ ከሆነ በሰወስትና አራት ወራት ዉስጥ ነዳጅ ዘይት ዳግም ማምረት ይጀመራል።»


የገንዘቡ ችግር፥ የዉጪዉ ግፊት፥ የአደራዳሪዎች ጥረትም ተደማምረዉ ሁለቱ ሱዳኖች አሁን ከደረሰቡበት መድረሳቸዉ ብዙ ታዛቢዎች እንደሚሉት ከሱዳኖች አልፎ ላካባቢዉም ሠላም ጠቃሚ ነዉ።ይሕ ማለት ግን ዶክተር ኦኬኬ እንደሚሉት ጠብ ቁርቁሱ አበቃ ማለት አይደለም።

«ታቦ ኢምቤኪ በሚመሩት የሱዳን የአደራዳሪዎች ቡድን አማካይነት ሠፊ ድርድር ቢደረግም፥ ድርድሩ ባንድ ወይም በሌላ ወገን ከስምምነት ይደርሳል ተብሎ ቢታሰብም፥ አሁንም ብዙ አጠራጣሪ ጉዳዮች አሉ።በሁለቱ ወገኖች መሐል መተማመን ገና አልሰፈነም።በዚሕም ምክንያት መሪዎቹ ለመሠረታዊ ስምምነት የሚያበቃ ዉሳኔ ማሳለፋቸዉን አጠያያቂ ያደርገዋል።»

ሁለቱ መሪዎች አዲስ አበባ ላይ የሚወያዩት ሱዳኖች ልዩነታቸዉን በድርድር እንዲያስወግዱ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት ለሁለተኛ ጊዜ የሰጠዉ ቀነ-ገደብ ባበቃ ማግስት መሆኑ ነዉ።ዕሁድ።

ሳልቫኪርምስል Reuters

ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ


ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW