1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ውጤት በየጣቢያዎች ይፋ ተደርጓል

ሐሙስ፣ ኅዳር 11 2012

የሲዳማ ክልል የመሆን ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ ውጤቶች ዛሬ በየምርጫ ጣቢያዎች ይፋ ተደርጓል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የህዝበ ውሳኔውን የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት ከ24 እስከ 48 ሰዓት ባለው ጊዜ እንደሚያስታውቅ ትላንት ምሽት ቢገልጽም እስካሁን ድረስ ውጤቱን አላሳወቀም።

Äthiopien Sidama Referendum
ምስል Getty Images/AFP/M. Tewelde

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ውጤቶች በየጣቢያዎች ይፋ ተደርገዋል

This browser does not support the audio element.

የሲዳማ ክልል የመሆን ጥያቄ ህዝበ ውሳኔ ጊዜያዊ ውጤት በየምርጫ ጣቢያዎች ተለጥፎ መራጮች ዛሬ ከንጋቱ ጀምሮ ውጤት እየተዘዋወሩ ሲመለከቱ ውለዋል። ለዚሁ አላማ ተተክለው የነበሩ ድንኳኖችም መነሳት ጀምረዋል። 

ዛሬ መግለጫ የሰጡት የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የሃዋሳ ከተማ መስተዳድር ከንቲባ “ውጤቱ ምንም ይሁን ምንም፤ ዋናው ጉዳይ ሰላም እና ተቻችሎና ተከባብሮ መኖር በመሆኑ ምንም ስጋት ሊኖር እንደማይገባ አሳስበዋል። በትላንትናው ዕለት የተካሄደው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት በሰላም በመጠናቀቁም ለህዝቡ ምስጋና አቅርበዋል።

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ። 

ሰለሞን ሙጬ

ተስፋለም ወልደየስ 
ማንተጋፍቶት ስለሺ 
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW