ሰሞነኛው የሳውዲ ፍተሻ አፈሳ
ሐሙስ፣ የካቲት 12 2012ማስታወቂያ
ካሳለፍናቸው ሳምንታት ወዲህ የሳውድ አረቢያ መንግሥት ፖሊስ እና የደህንነት አካላት ከፍተኛ የሆነ ፍተሻ በማካሄድ ላይ ናቸው። በሳውዲ መንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች የሚካሄደው የፍትሻና የቤት ሰበራ ዘመቻ ሁሉን የውጭ ዜጎች ያካተተ ቢሆንም ኢትዮጵያውያን ጨምሮ የጥቂት ሃገራት ዜጎች ላይ ብቻ ያተኮረ ነው መባሉ ስጋት መፍጠሩን ከጂዳ ነብዩ ሲራክ የላከልን ዘገባ ያስረዳል። ፍተሻውን በሚመለከት ከሚሰራጩ መረጃዎ ጎን ለጎን ከዚህ ቀደም የተለቀቁ መረጃዎች እንደ አዲስ በማህበርዊ መገናኛው መድረክ በሰፊው መሰራጨታቸው በስላማዊ መንገድ ሰርቶ የሚኖረውን ዜጋም ሳይቀር ስጋት ላይ መጣላቸውንም አመልክቷል።
ነቢዩ ሲራክ
ሸዋዬ ለገሠ
ኂሩት መለሰ