የስልክና ኢንተርኔት አገልግሎት ስርጭት
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 4 2005ማስታወቂያ
የሀገሪቱ ሽቦ አልባ የኢንተርኔት ሽፋን ማደጉም ተነግሯል። አሁን አሁን በትላልቅ ከተሞች ብቻ ሳይሆን በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተንቀሳቃሽ ስልክን መገልገል እንደ ቅንጦት መታየቱ የቀረ ይመስላል። ባለፈው ሰኞ በአዲስ አበባ በተጀመረው የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ የሥራ ፈጣሪነት ጉባኤ ላይ የተነገረውም ይህን በከፊሉ ያረጋገጠ ይመስላል።
የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር ገብረጺዮን ገብረሚካኤል እንዳሉት የሞባይል አገልግሎት ተጠቃሚዎች 18 ሚሊዮን ደርሰዋል። በሁለት ዓመት ውስጥ 45 ሚሊዮን የሞባይል ተጠቃሚዎች በኢትዮጵያ ይኖራሉ። ከሞባይል አገልግሎት መስፋፋት ጋር ተያይዞም የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር ከሶስት ሚሊዮን በላይ መድረሱን ሚንስትሩ አክለው ገልጸዋል።
ገመቹ በቀለ
ሂሩት መለሰ