የስኳር ፕሮጀክቱ ቀዉስ
እሑድ፣ ግንቦት 14 2008ማስታወቂያ
የስኳር ፕሮጀክቱን ለማስፈጸም ኃላፊነት የተሰጠዉ የኢትዮጵያ የስኳር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች የሥራ አፈጻጸም ዘገባ ከታቀደዉ የአንዱም ፋብሪካ ሥራ ሳይጠናቀቅ ብድር የመክፈያዉ ወቅት መድረሱን ለምክር ቤቱ አርድቷል። በሀገር ዉስጥ የስኳር እጥረት መኖሩ እና ዋጋዉ መናሩ በሚነገርበት በዚህ ወቅት ፋብሪካዎቹ ተጠናቀዉ ወደ ስኳርነት ይለዉጡታል ተብሎ የተተከለዉ አገዳ ደርሶ ወደ መበላሸት መቃረቡም ይነገራል። የተቆጠርና ገና ያልተቆጠረ ገንዘብ ብክነት የገጠመዉ ፕሮጀክት የዚህ ሳምንት የዶቼ ቬለ የእንወያይ ርዕስ ነዉ። ዉይይቱን ከድምጽ ዘገባዉ ያድምጡ።
ሸዋዬ ለገሠ
ማንተጋፍቶት ስለሺ