1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«ኢትዮጵያዉያኑ በሰላም እንዲመለሱ እየጣርን ነዉ» የጂዳ ቆንስላ

ዓርብ፣ ሰኔ 16 2009

የስዑዲ አረብያ መንግሥት በሃገሪቱ ያለ ሕጋዊ ፈቃድ የሚኖሩ የዉጭ ሃገር ዜጎች  እንዲወጡ ያስቀመጠዉ ቀነ-ገደብ  ሳያራዝም አይቀርም የሚል ወሬ እየተናፈሰ ነዉ።ይሁንና  በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽፈት ቤት እንዳስታወቀዉ ወሬዉን ከሕጋዊ ምንጭ ማረጋገጥ አልተቻለም።

Saudi Arabien Dschidda
ምስል Getty Images/AFP/K. Saad

M M T/ Exk.Inter.mit Botschafter Wubhet Demissie in Jeddah über Saudi Rückkehrer - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

በስዑድ አረብያ ያለ ሕጋዊ ፈቃድ የሚኖሩ አንዳድ ኢትዮጵያዉያን ደግሞ የመንን ወደ መሳሰሉ ሃገራት ከመፍለስ ይልቅ ወደ ሃገራቸዉ ቢመለሱ እንደሚሻል ቆንስላዉ  ምክር ለግሶአል።

የሳዑዲ አረቢያ መንግስት ያስቀመጠዉ  ቀነ ገደብ ፤ ሊራዘም ይችላል ነገ መግለጫ ይወጣል የሚለዉ ተናፋሽ ወሬን ማረጋገጥ አይቻልም ፤ በስዑዲ መንግሥት በኩልም የምሕረት አዋጁ እዚህ ጋር ይቆማል ተብሎ መግለጫ አልተሰጠም ሲሉ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽፈት ቤት ኃላፊ አምባሳደር ዉብሸት ደምሴ ተናግረዋል።

ቆንፅላ ጽ/ቤቱ መመለስ ለሚሹ ኢትዮጵያዉያን ሰነድ ከመስጠት ባሻገር ትራንስፖርት እንዲያገኙ ሁሉ ጥረት እያደረገ መሆኑም ታዉቋል።

በስዑድ አረብያ ሕገ-ወጥ የተባሉት ኢትዮጵያዉያንን ለማጓጓዝ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ የባሕር መስመር የሚያቀርብ አካል ካለ እድሉን ሰጥተናል ሲሉም  አምባሳደር ዉብሸት ደምሴ ተናግረዋል።

መንግስት ወደ ኢትዮጵያ ለሚመለሱ ዜጎች የተለያዩ ጥቅሞችን ይሰጣል ። በዚህም ከስዑዲ አረብያ የሚፈናቀለዉ ኢትዮጵያዊ ወደ ሃገሩ ወደ ወገኑ ቢገባ እመክራለሁ ሲሉ አምባሳደር ዉብሸት ደምሴ ገልፀዋል።

አዜብ ታደሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW