1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማሊያ ሰብዓዊ ቀውስ

ዓርብ፣ ጥቅምት 22 2000

«ሁኔታው በጣም አሳሳቢ ነው ። በመቅዲሾ ከፊል በተካሄደው ከባድ ውጊያ ምክንያት ባለፈው ሳምንት ብቻ ዘጠና ሺህ ተጨማሪ ሰዎች ተፈናቅለዋል ። » በሶማሊያ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ተጠባባቂ አስተባባሪና የተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ ተወካይ ክርስቲያን ባልስሌቭ

የጎዳና ላይ ውጊያ በሶማሊያ
የጎዳና ላይ ውጊያ በሶማሊያምስል AP

በሰሞኑ የሶማሊያ መዲና መቅዲሾ ውጊያ ምክንያት በርካታ ሰላማዊ ሰዎች መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ ። ድርጅቱ ትናንት ይፋ እንዳደረገው በሰሞኑ ውጊያ የተፈናቀሉት ሶማሊያውያን ቁጥር ሰማንያ ስምንት ሺህ ይደርሳል ። ቀድሞ በተፈናቀለው ላይ የተጨመረውን የአሁኑን ተፈናቃይ ለመርዳት የዕርዳት ድርጅቶች የበኩላቸውን እየጣሩ ነው ። ሆኖም በሶማሊያ የሚንቀሳቀሱ የተባበሩት መንግስታትም ሆነ ሌሎች የረድኤት ድርጅቶች የሚገባቸውን ያህል ችግር ላይ ለወደቀው ህዝብ መድረስ አልቻሉም ። ለዚህም የኦቻ ሶማሊያ ሀላፊ ለተፋላሚ ወገኖች ጥሪ አድርገዋል ።

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW