1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶማሊያ ካቢኔ ሹምሽር

ሰኞ፣ ሰኔ 28 2002

ከሚሊሺያ ቡድን ሁለት ሚኒስትሮች ተሹመዋል። አዲሱ ካቢኔ በሶማሊያ ምክር ቤት መጽደቁ አጠራጣሪ በሆነበት በአሁኑ ጊዜ በአህሉ ሱኒ ዋል ጀማ ቡድን ውድቅ ተደርጓል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ሸርማርኬምስል AP

ጠቅላይ ሚኒስትር ኦማር አብዲረሺድ ዓሊ ሼርማርኬ ሦስት ወራት የወሰደባቸውን የሹም ሽር ውሳኔ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ተግባራዊ ሲያደርጉ የሶማሊያ ቀጣይ ዕጣ ፈንታ ወደ ሰላሙ ያመራ ይሆን --የሚል ተስፋ በብዙዎች ዘንድ አጭሮ ነበር። የካቢኔ ሹምሽሩ በሸርማርኬና በፕሬዝዳንቱ በሼክ ሸሪፍ መሓል ያለውን የሻከረ ግንኙነትንም ሳያለሳልሰው እንዳልቀረ ተገምቷል። በዚህ የካቢኔ ሽግሽግ ሁለት ተደማጭነት ያላቸው ለዘብተኛ የሚሊሺያ መሪዎች በሚኒስትርነት ተሹመዋል።የአህሉ ሱኒ ዋል ጀማ ቡድን አባል የሆኑት ሁለቱ ሰዎች አዲሱን ካቢኔ ተቀላቅለዋል። ጋዜጠኛ ሞሀመድ ሐጂ አብዲኑር እንደሚለው ግን አዲሱ ካቢኔ ገና በምክር ቤት የሚገጥመው ፈተና እያለ ከሱኒ መሪዎች የደረሰበት ተቃውሞ የካቢኔውን ስኬታማነት አጠራጣሪ አድርጎታል። አህሉ ሱኒ ዋል ጀማ በአዲሱ ካቢኔ የተካተቱት ሁለቱ ሰዎች አንደማይወክሉት ገልጿል።

መሳይ መኮንን

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW