ፕሬዝደንቷ የለቀቁት የሶማሌ ክልል
ማክሰኞ፣ ነሐሴ 1 2010![Somali Äthiopien Shinile-Zone Dürre erschwert Lebensbedingungen](https://static.dw.com/image/19238139_800.webp)
ማስታወቂያ
ይህን የገለፁት ክልሉን ወክለው የፌደራል ምክር ቤት አባል የነበሩት እና አሁን በስደት የሚገኙት አቶ ጀማል ዲሪዬ ኸሪፍ ናቸው። ለሁለት የአገልግሎት ዘመን ተመርጠው በጥቅሉ ስድስት ዓመት ከመንፈቅ በምክር ቤት የሶማሌ ክልል የሕዝብ ተወካይ የነበሩት አቶ ጀማል፤ በክልሉ ነገሮች የሚያመሩበትን አቅጣጫ በመረዳታቸው ለመሰደድ መገደዳቸውን ለዶይቼ ቬለ ገልጸዋል። አብዲ ኢሌ በመባል የሚታወቁት የሶማሌ ክልል ፕሬዝደንት ትናንት ከስልጣናቸው መልቀቃቸው ተነግሯል። ፕሬዝደንቱ አቤቱታ ሲቀርብባቸው መቆየቱን በማንሳት ከአቶ ጀማል ጋር አችር ቃለ ምልልስ አድርገናል። ፕሬዝደንቱን ለዚህ ያበቃቸው ግፊት ኖሮ ይሆን በሚል ላስቀደምኩት ጥያቄ ምላሽ በመስጠት ይጀምራሉ።
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ