የሶሪያ ተኩስ አቁም
ማክሰኞ፣ መስከረም 3 2009ማስታወቂያ
የሶሪያን ተፋላሚ ሐይላት የሚረዱት ዩናይትድ ስቴትስና ሩሲያ በሳምንቱ ማብቂያ ያወጁት ተኩስ አቁም እስካሁን ከሞለ ጎደል ተግባራዊ መሆኑ እየተዘገበ ነዉ።የተለያዩ መገናኛ ዜዴዎች እንደዘገቡት ከትናንት ጀምሮ ገቢራዊ የሆነዉ ተኩስ አቁም አልፎ አልፎ ቢጣስም በአብዛኞቹ አካባቢዎች የተኩስ ልዉዉጡ እንደቆመ ነዉ።የተኩስ አቁም ሥምምነቱን የሶሪያ መንግሥት ሙሉ በሙሉ ሲቀበለዉ በምዕራባዉያንና በአረብ ሐገራት የሚደገፉት አማፂያን ግን ስምምነቱን ቢቀበሉትም ስምምነቱ ለሶሪያ መንግሥት ያዳላ ነዉ በማለት ሲያንገራግሩ ነበሩ።በዚሕም ምክንያት ስምምነቱ እንደከዚሕ ቀደሞቹ ስምምነቶቹ ሁሉ መፍረሱ አይቀርም የሚል ግምት አሳድሯል።የብራስልሱ ወኪላችን ዘገባ ልኮልናል።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ