1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሶርያ ውዝግብና የዓለም ሀገሮች

ረቡዕ፣ ግንቦት 22 2004

የሶርያ ልዩ ልዑክ የቀድሞው የተመድ ዋና ፀሐፊ ኮፊ አናን የሶርያ ፕሬዚደንት በሺር ኧል አሳድ አሥራ አምስት ወር የሆነውን ደም አፋሳሽ ውዝግብ ባስቸኳይ እንዲያበቁ አሳሰቡ። ባለፈው ዓርብ በሁላ ከተማ ቢያንስ አንድ መቶ ሰዎች የተገደሉበትን ርምጃ

In this image made from amateur video released by the Shaam News Network and accessed Monday, May 28, 2012, purports to show black smoke rising from buildings in Homs, Syria. U.N. envoy Kofi Annan called Monday on "every individual with a gun" in Syria to lay down arms, saying he was horrified by a weekend massacre that killed more than 100 people, including women and small children. (Foto:Shaam News Network via AP video/AP/dapd) TV OUT, THE ASSOCIATED PRESS CANNOT INDEPENDENTLY VERIFY THE CONTENT, DATE, LOCATION OR AUTHENTICITY OF THIS MATERIAL
ምስል dapd

በመቃወም ጀርመን፡ ፈረንሣይና በርካታ የአውሮጳ ህብረት ሀገሮች፡ እንዲሁም፡ ዩኤስ አሜሪካ፡ ካናዳ፡ አውስትሬሊያ፡ ቱርክና ጃፓን የሶርያ አምባሳደሮችና ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በሰባ ሁለት ሰዓት ሀገሮቻቸውን ለቀው እንዲወጡ አዘዋል። የዶይቸ ቬለ ባልደረባ ኡልሪኽ ላይድሆልት እንደሚለው፡ ምዕራባውያቱ ሀገሮች ይኸው ያጠናከሩት ግፊት የአሳድ መንግሥት በተቃዋሚዎች ላይ እየወሰደ ያለውን የኃይል ርምጃ እንዲያበቃ ማስቻሉን ብዙዎች ይጠራጠሩታል።

ትናንት በደማስቆ ከሶርያ ፕሬዚደንት በሺር ኧል አሳድ ጋ የተወያዩት የሶርያ ልዩ ልዑክ ኮፊ አናን የሶርያ መንግሥት ደም አፋሳሹን ግጭት አሁኑኑ እንዲያበቃ እና አሳድም ውዝግቡን ለማብቃት አናን ያዘጋጁትን ባለስድስት ነጥብ የሰላም ዕቅድ ተግባራዊ የማድረጉን ቆራጥ ርምጃ ነገ ሳይሆን ዛሬውኑ እንዲወስዱ አሳስበዋል። በውዝግቡ የሚፋለሙት የጦር ኃይሉና ተፋላሚ ሚሊሺያዎችም በጠቅላላ የኃይሉን ርምጃ እንዲያቆሙና የሰላሙን ዕቅድ እውን ለማድረግ የሚጠበቅባቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ በጥብቅ ጠይቀዋል። ይሁንና፡ በሁላ ከመቶ የሚበልጥ ሰው የተጨፈጨፈበት ድርጊት ግን ለሶርያ ውዝግብ በድርድር መፍትሔ ማገኘቱ ምን ያህል አዳጋች መሆኑን እንዳሳየ አናን ተገንዝበውታል።
« ይህ የሰላም መልዕክት ለመንግሥቱ ብቻ ሳይሆን፡ የጦር መሣሪያ ለያዛ ማንኛውም ግለሰብ ነው። ባለ ስድስት ነጥቡ አጠቃላይ የሰላም ዕቅድ ተግባራዊ መሆን አለበት። ግን ዛሬ ይህ እየሆነ አይደለም። »

በሰላሙ ዕቅድ መሠረት የተኩስ አቁሙ ደንብ ካለፉት ሰባት ሣምንታት ወዲህ ተግባራዊ ነው ቢባልም እና የተመድ ታዛቢ ቡድን በሀገሪቱ ቢሰማራም፡ በሶርያ ግድያው አላበቃም። በዚህም የተነሳ ጀርመን፡ ፈረንሣይና በርካታ የአውሮጳ ህብረት ሀገሮች፡ እንዲሁም፡ ዩኤስ አሜሪካ፡ ካናዳ፡ አውስትሬሊያ፡ ቱርክና ጃፓን የሶርያ አምባሳደሮችና ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ሀገሮቻቸውን ለቀው እንዲወቱ የሰባ ሁለት ሰዓት ጊዜ ሰጥተዋል። የሁላውን ዓይነት ግድያ ለማብቃት በሶርያ አንፃር ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እስከተስማማ ድረስ ወታደራዊ ርምጃ አይወሰድም ተብሎ እንደማይታሰብ የፈረንሣይ ፕሬዚደንት ፍራንስዋ ኦሎንድ አስታውቀዋል።
« ወታደራዊው ርምጃ ከጥያቄ ውጭ አይደለም። ዓለም አቀፉ ሕግ እስከተከበረ ድረስ። ማለትም የተመድ ፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ከመከረ በኋላ መሆን ይኖርበታል። እኔና ሌሎች ሩስያውያኑንና ቻይናውያኑን ማግባባት፡ እንዲሁም፡ መፍትሔ ማፈላለግ ይጠበቅብናል። ይህ መፍትሔ የግድ ወታደራዊ ርምጃ መሆን የለበትም። ግን የበሺር ኧል አሳድን መንግሥት ለማስወገድ በወቅቱ ግፊቱ መጠናከር ይኖርበታል። »
ምክር ቤቱ ወታደራዊ ርምጃ የሚወሰድበትን ውሳኔ ማሳለፍ ይችል ዘንድ ግን ሩስያ እና ቻይና ዕቅዱን እንዲደግፉ ማግባባት አስፈላጊ መሆኑን ኦሎንድ አመልክተዋል።
ይሁንና፡ ቻይና እና ሩስያ ምንም እንኳን የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ የሁላን ግድያ ያወገዘበትን ውሳኔ ቢደግፉም፡ በሶርያ አንፃር ማንኛውንም ወታደራዊ ርምጃ እንደማይደግፉ ግልፅ አድርገዋል። ይህ ዓይነቱ ውሳኔ ውዝግቡን ይበልጡን እንደሚያባብሰው የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትእር ሴርጌይ ላቭሮቭ ገልጸዋል።
« በምንወስደው ማንኛውም ርምጃ ላይ በጣም ጥንቃቄ ማድረግ ይገባናል። እሣት ላይ ነዳጅ ማርከፍከፍ የለብንም። በዚህ ፈንታ ውዝግቡን ማብረድና ተቀናቃኞቹን ወገኖች እንደገና ወደ ድርድሩ ጠረጴዛ እንዲመለሱ ማድረግ ይጠበቅብናል። »
በኃይል የሚደረግ የሥልጣን ለውጥን በጥብቅ እንደምትቃወምም ቻይና በተጨማሪ አስታውቃለች።
ልክ እንደቻይናና ሩስያም የዐረብ ሊግ አባል ሀገሮች ወታደራዊ ርምጃን አይደግፉም። እስካሁን አንድም የሶርያን ዲፕሎማት ከሀገራቸው አላስወጡም።
በሶርያ ግድያው እንዳይቀጥል ለማከላከል ዲፕሎማቲኩን ግፊት ከማጠናከር የተሻለ ሌላ አማራጭ እንደሌለ ነው የገለጹት።

ሴርጌይ ላቭሮቭምስል AP
ፍራንስዋ ኦላንድምስል picture-alliance/dpa
ምስል picture-alliance/dpa

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW