1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሼክ መሐመድ አል-አሙዲ ቀድሞ ከነበሩበት ቅንጡ ሆቴል ተዛውረዋል

ዓርብ፣ ጥር 25 2010

ሚድል ኢስት ሞኒተር የተባለው ድረ-ገፅ እንደዘገበው የሼክ ሙሐመድ አል-አሙዲ ቤተሰቦች ለእስር የተዳረጉት የ71 አመቱ ባለወረት ገንዘብ እና ንብረታቸውን ለማስረከብ አሻፈረኝ በማለታቸው ነው። በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው የዶይቼ ቬለ ወኪል ስለሺ ሽብሩ እንደሚለው ግን መረጃው የተሳሳተ ነው።

Ritz-Carlton in Saudi Arabien
ምስል picture-alliance/augenklick/firo Sportphoto/El-Saqqa

የሼክ መሐመድ አል-አሙዲ ቤተሰቦች ጉዳይ

This browser does not support the audio element.

በሳዑዲ አረቢያ መንግሥት የጸረ-ሙስና ዘመቻ በእስር ላይ የሚገኙት ሼክ ሙሐመድ አል-አሙዲ ቤተሰቦች ታስረዋል የሚል ወሬ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ገደማ ተሰምቶ ነበር። ሚድል ኢስት ሞኒተር የተባለው ድረ-ገፅ እንደዘገበው የሼክ ሙሐመድ አል-አሙዲ ቤተሰቦች ለእስር የተዳረጉት የ71 አመቱ ባለወረት ገንዘብ እና ንብረታቸውን ለማስረከብ አሻፈረኝ በማለታቸው ነው። በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው የዶይቼ ቬለ ወኪል ስለሺ ሽብሩ እንደሚለው ግን መረጃው የተሳሳተ ነው። ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ የሚገኘው ስለሺ ከአስራ አንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት ሐብት ባለቤት የሆኑት አል-አሙዲ ቀድሞ ከነበሩበት ቅንጡ ሆቴል መዘዋወራቸውን ተናግሯል። ሳዑዲ አረቢያ በሙስና የጠረጠረቻቸውን ልዑላን እና የናጠጡ ባለወረቶች ለወራት ከተካሔደ ምስጢራዊ ድርድር በኋላ መፍታት ጀምራለች።  
ስለሺ ሽብሩ
እሸቴ በቀለ
ኂሩት መለሰ 
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW