የሽታይንማየር የአፍሪቃ ህብረት ጉብኝት
ረቡዕ፣ ጥር 22 2011![Besuch von Bundespräsident Steinmeier in Äthiopien](https://static.dw.com/image/47289379_800.webp)
ማስታወቂያ
የጀርመን ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር በኢትዮጵያ ያደረጉትን የ3 ቀናት ጉብኝታቸውን ዛሬ አጠናቀው ወደ ጀርመን እየተመለሱ ነው። ፕሬዝዳንቱ ዛሬ እኩለ ቀን ላይ ከአዲስ አበባ ለመነሳት ቢያቅዱም አውሮፕላናቸው ባጋጠው የቴክኒክ ችግር ምክንያት ጉዞአቸው እንዲዘገይ መደረጉ ተዘግቧል።ሽታይንማየር ዛሬ ጠዋት በአፍሪቃ ህብረት ኮሚሽን በመገኘት ከህብረቱ ባለሥልጣናት እና ሠራተኞች ጋር የሀሳብ ልውውጥ አድርገዋል። የህብረቱ ቃል አቀባይ ለDW እንደተናገሩት ሽታይንማየር የጀርመንን እና የአፍሪቃ ህብረትን ትብብር የማሳደግ ፍላጎት አላቸው። የጀርመን መንግሥት በአፍሪቃ ህብረት አማካይነት የአባል ሀገራት ልማትን ሊያፋጥኑ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ እየሰራ መሆኑንም ቃል አቀባይዋ ተናግረዋል። ያነጋገራቸው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ