1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የቀድሞ የጦር መኮንን አስተያየት

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 2 2014

ኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስቴር ትናንት በፌስ ቡክ ገፁ  ባወጣዉ መግለጫ ግን "ሠራዊቱ በራሱ እቅድ ሙሉ ማጥቃት ከጀመረ 'ተጠቃሁ' ብሎ ለመናገር ጊዜ እንኳን ሳያገኝ የሚፈፀም እንደሚሆን መታወቅ አለበት" ብሎ ነበር። መግለጫዉ ዛሬ ከየገፁ ተነስቷል ወይም ተሰርዟል።

ፎቶ ከክምችት
ፎቶ ከክምችትምስል፦ Ethiopian News Agency/AP/picture alliance

የኢትዮጵያ ጦር አዲስ ከፈተዉ የተባለዉ ጥቃትና የቀድሞ መኮንን

This browser does not support the audio element.

ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ሕወሓት) «ተከፈተብኝ» ያለዉን  ጥቃት የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን በይፋ አላረጋገጠም።ይሁንና የጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ ቃል አቀባይ ቢልለኔ ስዩም አሶስየትድ ፕረስ ለተባለዉ ዜና አገልግሎት፣ ሕወሓት በአማራና በሌሎች አካባቢዎች ያደርሰዋል ያሉትን ጥፋት፣ጥቃትና ግድያን ለማስቆም የኢትዮጵያ መንግስት መጣሩን ይቀጥላል ብለዋል።ቃል አቀባይዋን በስልክ ለማግኘት በተደጋጋሚ ብንሞክርም ስልካቸዉን አይመልሱም።የሕወሓት ቃል አቀባይን ለማነጋገር ያደርግነዉ ሙከራም አልተሳካም።የኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስቴር ትናንት በፌስ ቡክ ገፁ  ባወጣዉ መግለጫ ግን "ሠራዊቱ በራሱ እቅድ ሙሉ ማጥቃት ከጀመረ 'ተጠቃሁ' ብሎ ለመናገር ጊዜ እንኳን ሳያገኝ የሚፈፀም እንደሚሆን መታወቅ አለበት" ብሎ ነበር። መግለጫዉ ዛሬ ከየገፁ ተነስቷል ወይም ተሰርዟል።

ሰለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW